የቤተክዋክብቱ ጋሻጃግሬዎች - ቅጽ - ፩ (ፊልም እስክሪፕት ትርጉም) Guardians of the Galaxy Vol 1 Transcript in Amharic

የቤተክዋክብቱ ጋሻጃግሬዎች ቅጽ፦ ፩

ጋርዲያንስ ኦፍ ዘ ጋላክሲ፦ ቅጽ. 1

Guardians of the Galaxy፦ vol. 1)

፪፻፻፲፬ እኤአ.፣ በ ጀምስ ጉን የዘመተ (ዳይሬክትድ) ፊልም፣ ማርቭል ቧልታይ (ኮሚክስ) ኅዋ፤


የመላሹ መግቢያ

የተወዳጁ ጀምስ ጉን ፊልም፣ ከምንጊዜውም ምርጥዎቹ አንዱ ነው። ቧልትአዊ አፈጋጊነቱ ድንቅ ጠረፍ እንደደረሰለት ከዘመንአችን ቧልታይ (ኮሚክ) መር ፊልምዎች ቁንጮው ነው። ቢያንስ ይህን ሳይሉ ብዙዎች እሚቀሩ አይደሉም። በያዘው ትርክት እንድትዝናኑ ጀምስ ጉን በ ፪፻፻፲፬ እኤአ. ወደ ተንቀሳቃሽ ምስል የመለሰውን ፊልም እስክሪፕት ከእንግሊዝኛ ቅጂው ወደ አማርኛ ለማዉጣት ሞክሬያሁ። ከብረት ዝገት ነው እና ለስህተትዎቼ ከወዲሁ ይቅርታ።

ከትርጉሙ ሰውነት አንፃር፣ በማንኛውም መልኩ፣ በአዉቆታ ክፉ ያልሆነ ማንም ሰው፣ የትርጉም ሰውነቱን ለፈለገው አላማ ሁሉ መቅጠር ይችል ዘንድ ስለፈቀድሁ ይሁን። ለምሳሌ በፊልሙ ንዑሠርእስ (ሰብታይትል) አድርጎ መጠቀም እሚቻል ነው። ወይም ማንበብ እና መዝናናት እሚችል ነው። (ለንዑሠርእስ እና ማንበቡ ግን ያጠሩ እና የተለጠጡ፣ እንደቅደምተከተልአቸው፣ ሁለት ልዩ ቅጅዎች እያዘጋጀሁ ነው። ለእነዛ አሽከርነት በልዩነት እሚሻሉ ቅጅዎቹን መጠቀም እመክር አለሁ)።

የእዚህ ትርጉም እስክሪፕት አጠቃቀሙ፣ በተጠቃሚው ኃላፊነት እንደሆነ ግልጥ የለሁበትምታ (ዲስክሌመር) እነሆበእዚህወዲአ (ናውሂርባይኦን) ታደለ። የለሁበትምታ ካልዕ እሚሆነኝ ደግሞ፦ ይህ ይፋ የቋንቋ ምለሳ አይደለም ብዬ ማወጄ ነው። ይልቁንም፣ ይህ ትርጉም የስክሪፕት ሰዉነት፣ ከእየድረገጾቹ ሰባስቤ ለምርጥነቱ ያዉጣጣሁለት ማለትእሚቻል ነው። የግሌ አያያዝም ተቀንጭቦ የተለጠፈበትም ሁሉ ነው። በይፋ ማርቭልዎች ወይም ጀምስ ጉን እንድመልስ ያደረጉኝ አይደለም እና የእነእርሱን ስራ በይፋ የተረጎመ አይደለም። ይህእንዲህ በእንዲህ እንዳለን፣ ለኢንዶኔዢያአዊው ፖፒ ኤንጅል እና ፋንዶም.ኮም (www.fandom.com) የፊልሙ ስክሪፕት ቅጅዎችአቸው ምስጋናዬ ተቻዩ ትልቅ ነው። በደግ መጠን እንደተመለሰ አምን ዘንድ አለሁ እና ይፋ ባይሆንም ማንም ቢጠቀመው መደበኛነት እንጂ ይህቀረሽ እሚባለው ጉድለት ግን አያሰጋውም። መልካም ንባብ ወይም አገልግሎት ይሁን-እላችሁ’ አለሁ። አመሰግናለሁ፨

ቢንያም ኃይለመስቀል ኪዳኔ፣ ፪፻፻፲፪ ጳጉሜ፣ ከተማ-ወልቂጤ፣ ኢትዮጵያ፨

www.bnyam-El.blogspot.com; Binyamael@gmail.com 

ትልም አንድመስመሬ (ፕሎት ዋንላይነር)

በእየፊናአቸው ሩር (ኦርብ) በማሳደድ የተዋወቁ ልዕለጀግናዎች (ሱፐርሂሮስ) አስጊውን ገሃድ፦ የቤተክዋክብቱ ኑባሬ (ኤግዚስተንስ) አደጋ ላይ እንደወደቀ፣ ድንገት ይረዱ አሉ፨

የቤተክዋክብቱ ጋሻጃግሬዎች


ምድር ፲፻፹፬ እኤአ.


[ታዳጊ ፒተር (ጴጥሮስ) ክዊል በቤተመስተናገጃዉ (ሆስፒታል) ኮሪደሩ ላይ ነው። “ድንቅ ዉህድ” እሚለውን ቅረጽአጫውቴ (ቴፕ) በወክማኑ ስር እያደመጠ ነበር። አያቱ ወደ እርሱ ቀረበ]

አያት (ግሬግ ሄንሪ)

ጴጥሮስ?

እናትህ ልታናግርህ ትፈልግህ አለች።

ና እሺ ፒተ።

እኒህን ጅል ነገርዎች አዉጣ።

[የቅረጽአጫውቴው ዉህዱን ከጴጥሮስ ወሰደ። ወክማኑን አጠፋ። ጴጥሮስ እናቱን እንዲመለከት ወሰደው። እርሷም እጅግ ታምማ በሞትአልጋዋ የተነጠፈች የነበረች ናት፣ የተጠበጠበ ዓይኑን አስተዋለች]

ሜሪዴት ክዊል (ሎዉራ ሀዶክ)

ለምን ድጋሚ ከሌላዎቹ ልጅዎች ስትጣላ ነበር፣ አቢ?

[ጴጥሮስ ትከሻውን በእንቢታ ወዘወዘ]

ጴጥሮስ?

ታዳጊ ጴጥሮስ ክዊል (ውያት ኦሌፍ)

አንድ ትንሽዬ እንቁራሪት ገደሉ እሱ ምንም ነገር አላደረገም፤

በዱላ ዠለጡት።

ሜሪዴት ክዉዊል (ሎውራ ሀዶክ)

[ሣቀች]

በጣም የአባትህ ብጤ ነህ። እርሱን ትመስልአለህ ሁሉ።

እሱም እንዲሁ መልአክ ነበር። ከንጹህ ብርሃን የተቀመመ።

[የሜሪዴት ዓይኖች ለቅጽበቶች ተጨፈኑ]

አያት (ግሬግ ሄንሪ)

ሜር? እሱጋር ለጴጥሮስ ሥጦታ አለሽ አደል፣ የለሽም?

ሜሪዴት ክዊል (ሎዉራ ሀዶክ)

አው እንጂ። ይኸው።

[የተጠቀለለውን ትንሽ ሥጦታ እና ካርድ ነካ አደረገች፣]

አያት (ግሬግ ሄንሪ)

እኔ አስተካክልልህ አለሁ፣ ፒተ።

[አባቷ ሥጦታዎቹን ወሰደ እና በጴጥሮስ ጀርባሸክም ጨመረአቸው]

ሜሪዴት ክዊል (ሎዉራ ሀዶክ)

እምትከፍተው እኔ ስሄድ ነው፣ እሺ?

[የጴጥሮስ ዓይኖች እንባ አቀረሩ]

አያትህ ምርጥ እሚባል እንክብካቤ ያደርግልህ አለ።

ቢያንስ አባትህ ሊያገኝህ ተመልሶ እስኪመጣ።

እጄን ዉሰድ።

[እጇን ከፈተች ግን ጴጥሮስ በእንቢታ ሆነ፤ ማልቀስ ጀመረ]

አያት (ግሬግ ሄንሪ)

ፒተ፣ በል እንጂ።

ሜሪዴት ክዊል (ሎዉራ ሀዶክ)

እጄን ዉሰድ።

[ልክ ያኔ የልብምቷ ይቋረጥ እና ትሞታለች]

ታዳጊ ጴጥሮስ ክዊል (ውያት ኦሌፍ)

እማ? አይሆንም! አይሆንም! አይሆንም! አይሆንም! እማ! አይሆንም!

[ሐኪሞች እየተራወጡ ወደ ክፍሏ ዉስጥ ሲገቡ ሆነ]

አያት (ግሬግ ሄንሪ)

ከእኔ ጋር ና።

[አያቱ ከእናቱ በድን ፊት ይዞት ወደ አነሳው ኮሪደር መቀመጫ ሊመልስ አወጣው። ጴጥሮስ ግን አስቸገረ እና አካልአዊነት ተፈጠሮ ወጣ]

ታዳጊ ጴጥሮስ ክዊል (ውያት ኦሌፍ)

አይሆንም! አይሆንም!

አያት (ግሬግ ሄንሪ)

እዚህ መቆየት አለብህ። እባክህ።

ታዳጊው ጴጥሮስ ክዊል (ውያት ኦሌፍ)

አይሆንም...

አያት (ግሬግ ሄንሪ)

እሺህ?

[ጴጥሮስ ተመልሶ ወደ ክፍሉ ሲገባ አያቱን ተመለከተ፣ ከእዚያም ሮጦ ወደ ዉጭ እራሱን ያሻግር አለ። ሮጦ በጨለማው የሜዳ አካል በጉልበቱ ወድቆ ያነባ ዘንድ ሆነ]

ታዳጊ ጴጥሮስ ክዊል (ውያት ኦሌፍ)

[በድንገት አንድ ህዋመርከብ ከአናቱ በኩል ይገለጥ እና ባዕድአዊያን (መጤዓለሞች/ኤሊየንስ) ታፍኖ ይያዝ ዘንድ ሆነ]

[በድንጋጤ ጮኸ]

አይሆንም። እማ።

----


፳፮ ዓመትዎች ኋላ

ሞራግ

ባይተዋር ፈለኬ (ፕላኔት)


[ዐዋቂው ጴጥሮስ፣ ወደ ዋሻ እየገባ፣ በዉስጡ እሚገኘውን ትንግርተኛውን ሩር (ኦርብ) ያስስ አለ፣ ወክማኑን ያጠልቅ አለ። የሬድቦን “ከም ኤንድ ጌት ዩር ላቭ”ን እያደመጠ፣ አብሮ መዝፈን እና መደነስ ይጀምር አለ። ሩሯን ሲያገኝ፣ በታጠቁ ኮራት እና ግብረአበሮቹ ተደረሰበት]

ኮራት (ጂሞን ሆውንሱ)

ጣለው።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ኧ...እሺ።

[ኮራት ግብረአበሩን ጴጥሮስ ጋር ላከ]

ኮራት (ጂሞን ሆውንሱ)

ጣለው አሁኑኑ!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እንዴ፣ ወዳጄ። ምንም ችግር የለም። ምንም ችግር የለም ከቶ።

[ጴጥሮስ ሩሩን ጣለ፦ ልክ ሁለቱ ግብረአበሮች ደግነውበት ወደ እርሱ ቀረብ ሲሉ]

ኮራት (ጂሞን ሆውንሱ)

[ኮራት ሩሩን አነሣ] 

ስለእዚህ እንዴት አወቅህ?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ምን እንደሆነ እራሱ አላቅም። ጀንከር ብቻ ነኝ ሰውዬው። ብቻ...ብቻ ነገሮች እንዲሁ ዝምብዬ ስፈታትሽ ነበር።

ኮራት (ጂሞን ሆውንሱ)

ጀንከር እምትመስል አይደለህም። የለበስክው የራቬጀሮች ልብስ ነው።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ይሄ ዝምብሎ አለባበስ ነው፣ ሰውዬው።

[ከጎኑ ወደአለው አንዱ ዞረ]

ኒንጃ ዔሊ፣ እምትጎረጉረኝን ብትተው ይሻልህ አለ።

ኮራት (ጂሞን ሆውንሱ)

መኑ ስምከ ዉእቱ?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ስሜ ጴጥሮስ ክዊል ነው፣ እሺ?

ጓዴ፣ ፈታ በል።

ኮራት (ጂሞን ሆውንሱ)

ተንቀሳቀስ!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ስለምን?

ኮራት (ጂሞን ሆውንሱ)

ለአንተ ሮናን ጥያቄዎች ሊኖረው ይችል ዘንድ ይሆን አለ።

[ኮራት እዝ ሰጥቶ ሊመለስ ዞረ]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እሺ፣ ታውቅ አለህ? በሌላ መጠሪያ እምታውቀኝ ይሆን አለ። 

[ኮራት ዞረ፦ ጴጥሮስ ላይ ለመመልከት]

ኮከብ-ጌታ።

ኮራት (ጂሞን ሆውንሱ)

ማን?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ኮከብ-ጌታ፣ ሰውዬው። ልዕለዝነኛ ወንበዴ።

[ኮራት በግራመጋባት ትከሻ ነቀነቀ]

ሠዎች?

ኮራት (ጂሞን ሆውንሱ)

ተንቀሳቀስ!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አቦ፣ ተዉታ!

[ጴጥሮስ ጥይቱን መዠረጠ እና ሁለቱን ግብረአበሮች እና ኮራትን ተኮሰ። ልክ ሩሯን አንስቶ ሲነሳ፣ ጴጥሮስ ላይ መልሶ ተተኮሰበት። ያንን እንደምንም አቻቻለው። በወለሉ ወድቆ ብረት ባርኔጣውን አንቅቶ ለበሰ ፣ ጫማዎቹ እንደ ሮኬቶች ሆኑ እና ከዋሻው ወደዉጭ አስፈነጠሩት። ወደ መርከቡ ለመመስ  እንደምንም ሆኖ በቃ። እና የኮራት ግብረአበሮች ተከታትለውት ሲተኩሱበት እንዲሁ እያብቃቃ ለማምለጥ በመርከቡ ሆኖ ጀመረ። ወዲያው ቁጥጥሩ ጠፋበት እና በዉሥጡ ተንሳፈፈ። በመጨረሻ እቅጩ ጊዜ እየደረሰ ግን ለማስመለጥ መርከቡን አስቻለው። ወዲያው አንዲት እንስት ብቅ አለች]

በሪት (ሜሊያ ክሬይሊንግ)

ጴጥሮስ? ምን ተከስቶ ነው?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እሺ... ኧ...ኧ... እኔ...

[ጴጥሮስ መጠሪያዋን ያስታውሰው ዘንድ ተጣጣረ] 

በሪት (ሜሊያ ክሬይሊንግ)

በሪት።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

በሪት! እይ ፣ ካንቺጋር ሙሉበሙሉ ታማኝ ልሆን ነው። እዚህ እንደነበርሽ እረሳሁ።

[በድንጋጤ አፈጠጠችበት ፤ ኋላ ከሞራግ ርቀው ሲጓዙ ጴጥሮስ ዜናውን ገጽማያው (ስክሪን) ላይ ይመለከት ጀመረ] 

“ክሪ ግዛት ዉስጥ በወጣገባው የተነዙ ዐመጽዎች ዛሬ ፈነዱ፦ በክሪ ግዛትንጉሥ እና የዛንዳሯ ኖቫ ቀዳሚት መሀከል በቅርቡ የተፈረመውን ሰላም ሥምምነት በመቃወም።”

በሪት (ሜሊያ ክሬይሊንግ) 

[ዜናውን ሲያደምጥ በሪት ጥሪ ተመለከተች]

ጴጥሮስ፣ ጥሪ አጊንተህ አለ።

[በሪት ገጽማያውን ጠቅአደረገች እና ጥሪውን መለሰችለት] 

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አይሆንም፣ ቆይ፣ ተይ! 

[ማስቆም ሳያስችል፣ አጋሩ፣ ዮንዱ ገጽማያው ላይ ተገለጠ] 

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

ክዊል?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እሺ፣ ዮንዱ።

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

ነኝ እዚህ ሞራግ ዉስጥ። ምንም ሩር የለም፣ ምንም አንተም የለህ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ደህና፣ መንደሩ (ኔበርሁድ) ዉስጥ ነበርኩ። መንቀዋለሉን ልቆጥብልህ አስቤ ነበር።

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

ደግ፣ አሁን በየት ነው ያለህው፣ ልጅ?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ስለእዚህ የምር መጥፎነት ይሰማኛል፣ ነገርግን ያን እነግርህ ዘንድ የለም።

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

ይህን ጉዳይ ላስተካክል እንደባሪያ ፈግቼ ነበር።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ባሪያነት? ጥቂት ጥሪዎች መደወል “እንደባሪያ መፍጋት” ነው? ማለቴ፣ ከምር?

እና አሁን እኔን ልታከስረኝ ነው!

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

ያንን እርስለእርስ አናደርግም። እኛ ራቬጀሮች ነን። ምጢሬ (ኮድ) አለን።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ታዲያሳ። እና ያ ምስጢሬ “ስረቅ ከአገኘህው ሁሉ!” ነው።

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

ከ ታራ በአመጣሁህ ጊዜ ...

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

 “እሱ እኔን አመጣ”

[በሹፈት]

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

... እኒህ የኔ የሆኑት ልጆች ፈልገውህ ነበር ሊበሉህ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ኧረ?

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

ታራንአዊ ቀደም ብለው ቀምሰው አያውቁም ነበሩ።

እኔ አስቆምኩአቸው። ያንተ ህልውነት ምክንያቱ እኔ ነኝ!

አገኝህ ይሆን ዘንድ ነው። አገኝህ እና...

[ጴጥሮስ ዮንዱ ጋር እሚመላለስ ስልክ መስመሩን ዘጋው]

[ዮንዱ መርከብ ዉስጥ፣ ጴጥሮስን ልኮት (ሪፈረንስ) አድርጎ ዮንዱ መናገር ጀመረ]

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

ወሮታ አሠፍሩበት! አርባ ኬ። ዳሩ፣ እንዲደርሰኝ እምፈልገው በነብስ ሆኖ ነው።

አርባ ኬ።

ክራግሊን (ሲያን ጉን)

ታዲያስ፣ ሻም። (ሻምበል)

ሆሩዝ (ቶም ፕሮክተር)

ከነነብስ?

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

ያልኩት ያንን ነው።

ሆሩዝ (ቶም ፕሮክተር)

ነግሬህ ነበር፣ ያንን ልጅ ያነሣህ ጊዜ፣ ልናደርግ እንደተቀጠርንው ልናስረክበው ይሻል ነበር። ሸቀጥ (ካርጎ) ነበር! በእርሱ ጉዳይ ሁልጊዜም ላላ እንዳልክ ነህ።

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

አሁንስ ላላ እያልኩበት ያለሁት ብቸኛው አንተው ነህ! ለማንኛውም ግን፣ ስለ አቶ ክዊል አትጨነቁ። ተመልሶ እዚህ  ልክ እንዳገኘንው፣ እርሱን እኔው እገድልአለሁ። እና እኛ ልንጨነቅበት እሚገባን ቢኖር ፣ በእዚያ ማን ተጨማሪ ሩሩን እሚሻ ይኖር ይሆን አለ እሚለው ነው!


ጨለማ አስተሩ

የክሪ ዉጊያመርከብ


[በጦሯ ህዋመርከቡ፣ ሮናን እሚነሳ እና ደንገጡሮቹ እያለባበሱት እሚታይ ሆነ]

ሮናን (ሊ ፔስ)

“አሸባሪ” ብለው ይጠሩኛል፣ “አክራሪ”፣ “ጽንፈኛ”፣ “ቀናኢ”፣ ምክንያቱም፣ የህዝቦቼን፣ የክሪያዉያንን፣ ብሉይ ህግ ስለእማከብር፣ እንዲሁም ስለእምቀጣ የማያከብሩትን። ምክንያቱም የአባቴን፣ እና የሱን አባት፣ እና ከእሱ የቀደመውን አባቱን፣ ህይወት ስለነጠቃችሁ ለአንተ ህዝቦች ይቅርታ ስለእማላደርግ። የአንድ ሺህ አመቶች ጦርነት በመሀከልአችን የተደረገው ከቶ እሚረሳ አይደለም!

[ሮናን ትልቅ መሳሪያ አነሣ፣ ያም አንድ ዉጊያመዶሻ የሆነው የክሪዎች እዉቁ አንድ መሳሪያ ኮስሚ-ሮድ እሚሰኘው ነው]

ዛንዳርአዊው እስረኛ

አንተ ይህን ማድረግ አትችልም! የእኛ መንግስት የሠላም ስምምነት ፈርሟል።

ሮናን (ሊ ፔስ)

የኔ መንግስት ምንም ሀፍረት አያቅም። እናንተ ዛንዳሪያናዊያን እንዲሁም የእናንተ ባህል አንድ በሽታ ናቹህ።

ዛንዳርአዊው

አንተ ፈጽመህ ከቶ ዛንዳርን አትገዛም።

ሮናን (ሊ ፔስ)

አዎን። እፈውሰው አለሁ!

[ሮናን የወንዱን ራስቅል ወደታች ደሙ እስኪንዠረገግ በመሳሪያው መታው]

ነቢውላ (ኬረን ጂላን)

ሮናን፣ ኮራት ተመልሶ አለ።

[ኮራትን ሮናንን ተገናኘ]

ኮራት (ጂሞን ሆውንሱ)

ማስተር፣ ሌባ እኮ ነው፣ ወንበዴ እራሱን ኮከብ-ጌታ ብሎ እሚጠራ። ዳሩ፣ ዘ-ደላላ ተብሎ ለእሚታወቅ መሀሌ (ኢንተርሚዲያሪ) ሩሯን ሊለቅምለት ስምምነት እንዳለው መርምረን አግኝተን አለን።

ሮናን (ሊ ፔስ)

ለታኖስ ሩሩ ልለቅምለት ቃልሰጥቼ ነበር። ልክ ያኔ ብቻ፣ ዛንዳርን ይደመስስልኝ አለ።

ነቢውላ፣ ወደ ዛንዳር ዝለቂ። እንዲሁም ሩሩን ለኔ አግኝልኝ። 

ነቢውላ (ኬረን ጂላን)

ያ ለእኔ ክብር ይሆንልኛል።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

[ገሞራ እራሷን አቀረበች]

ያ ላንቺ ምጽዓትሽ ይሆንብሻል። ይህ ድጋሚ ከተከሠተ፣ አባትአችንን ካለሽልማቱ ልትተያዪው ይሆን አለ ማለት ነው።

ነቢውላ (ኬረን ጂላን)

እኔ የታኖስ እንስት ልጁ ነኝ። ልክ እንዳንቺ።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ዳሩ፣ እኔ ዛንዳርን አዉቅ አለሁ።

ነቢውላ (ኬረን ጂላን)

አስቀድሞ እኮ ሮናን አዉጇል እኔ...

ሮናን (ሊ ፔስ)

[ተቆጣት]

ለኔ አትናገሪልኝ! 

[ለ ገሞራ]

አንቺ አትወድቂም?

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

በፊትስ አዉቅ አለሁን?

----


ዛንዳር

የኖቫ ልዑለግዛት (ኢምፓይር) ዐምደከተማ


[ሮኬት እና ግሩት፣ ዛፍ-መሠል ሰብአማ (ሂዉማኖይድ)፣ በከተማው ዛንዳርአዊያኖች ላይ እየሰለሉ ነው]


ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ዛንዳርአዊያን። ምን ያሉ የተሸናፊዎች ስብስብዎች። ሁልአቸውም በቀዉጢ ችኮላ፣ ከሆነ ደደብነት ወደ ከቶ ዜሮነት ለመሻገር። ያሳፍራል! ይህን ሰው ተመልከቱ እስኪ!

[በእግረኛመስመር ወደእሚራመድ ከአጠረ ወርቅአማ ጸጉር ጋር ያለ ዛንዳርአዊን ልኮት እየሰጠ]

ታምኑትአላችሁ እኛን ወንጀለኞች ብለው ሲጠሩን? እሱ በዛ ጸጉር አቆራረጡ እሚያጠቃን ሆኖ ሳለ?

[በመራመድ ላይ ወደ ነበረ ትንሽዬ ዛንዳርአዊ ልኮት እያደረገ]

ይህ ምንድር ነገር ነው? እዩት እንዴት ቀዝቃዛ እንደሆነ እንደእሚያስብ። ድጋፍ ማግኘት ቀዝቃዛ አይደለም! ተራመድ ግልህን ችለህ! የሆንክ ጢኒጥ ጋርጎይል።

[ወደ አንድ አዛውንት (ስታን ሊ) እና አንዲት ሴት ልኮት እያደረገ]

እዩት እስቲ አቶ ፈገግፈገግን እዚህ ጋር። የት ነች ሚስትህ፣ ሽማግሌው? ምንያክል ደረጃ-ሀ ዋልጌ። ሃሃ ሃሃ ሃሃ.... አይደለ፣ ግሩት?

ግሩት?

[ግሩት በአቅራቢያው ከአለ አሸንዴ (ፋውንቴይን) መጠጥ እያደረገ ነበር]

የአሸንዴ ዉሃ አትጠጣ፣ አንት ቂል። ያ አስቀያሚ ነው!

[ግሩት ያልጠጣ እንደሆነ ለማስመሰል ብሎ አናቱን ነቀነቀ]

አዎን፣ አደረግህው፣ ስታደርገው ልክ መመልከቴ ነው! ስለምን ትዋሽ አለህ?

[“ቴት..ቴት..ቴት..”]

[አነጣጥሮ ሰው እያስመለከተ የሮኬት ጠሬ (ቴብሌት) ጢጥታ  አሰማው]

ዉህ! አንድ ያገኘን ይመስል አለ። እሺ፣ ብጤዬ (ሆሚ) የሆነ ሰው ሊያገኝህ እየፈለገ ያለው ምን ያክል ከልቡ ይሆን?

[ጠሬው ጴጥሮስ በሪትን እያዋራት ሳለ አትኩሮበት አስመለከተ፣ ሮኬት ወሮታ ጴጥሮስ ላይ እንደ ተለጠፈበት ተመለከተ፦ “ይፈለግ አለ: ጴጥሮስ ክዊል”]

፬፻፻፻ አሃዶች? ግሩት ከበርቴ መሆንአችን ነው።

[ሮኬት ወደ ግሩት ዞሮ ተመለከተ እና የአሸንዴውን ዉሃ ሲጎነጭ ደግሞ አገኘው። እህታ አሰምቶ አናቱን ወዘወዘ]

[ጴጥሮስ ዛንድር ዉስጥ በአንድ አንድ ሱቅ ገባ]

ዘደላላ (ክርስቶፈር ፌርባንክ)

አቶ ክዊል!?!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ዘደላላ። ሩሩ! ልክ በልዩ ትዕዛዙ መሠረት።

[ሩሩን አወጣ እና መቁጠሪያው ላይ ዘደላላው ፊት አስቀመጠ]

ዘደላላ (ክርስቶፈር ፌርባንክ)

የታል ዮንዱ?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እዚህ ሊሆን ፈልጎ ነበር። ፍቅሩንም ልኳል።

እና ነግሮኝ ነበር እንድነግርህ ፣ ገቢያው ዉስጥ ምርጦቹን ቅንድብዎች እንደያዝህ። 

[ተናደደ ዘደላላው እና በንቀት አለፈ]

ምንድር ነው ይሄ?

[ዘደላላ ሩሯን አነሣ]

ዘደላላ (ክርስቶፈር ፌርባንክ)

ደንበኞቼን ወይም ፍላጎቶቻቸውን አለማወያየት ትልምአግጣጫዬ (ፖሊሲ) ነው።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እና፣ ደህና፣ ላንተ ልለቅምልህ በእሚል ሞቼ ነበር ማለት ይቻላል።

ዘደላላ (ክርስቶፈር ፌርባንክ)

የሥራቦታ አደጋ፣ እርግጠኛ ነኝ፣ በሥራህ መስመር ዉስጥ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

የሆነ የአንቀሳቃሽ (ማሽን) አናትአማ ጉድ፣ ሮናን ለእሚሉት እሚሰራ ጓዴ።

ዘደላላ (ክርስቶፈር ፌርባንክ)

[ድንገት ዘደላላ ክው አለ] 

ሮናን? ይቅርታህን፣ አቶ ክዊል! ከምር አዝን አለሁ። ዳሩ፣ ሮናን የተካተተበት ከሆነ የእዚህ ልዉዉጥ ምንም አካልን አልፈልግም።

[ሩሩን ለጴጥሮስ መለሰለት እና ወደ ሱቁ በር ይገፈትረው ጀመረ] 

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ዎው! ዎው፣ ዎው፣ ዎው! ማንነው ሮናን?

[ዘደላላው ዳግ-ይገፋው ዘንድ  ቀጠለ] 

ዘደላላ (ክርስቶፈር ፌርባንክ)

የክሪ ወግአጥባቂ፣ በሰላም ስምምነቱ የተበሣጨ፣ የዛንዳርአዊያን ባህል፣ የእኔ ባህል፣ ከህላዌ እስኪፋቅ እማያርፍ የሆነ!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ና እንጂ።

ዘደላላ (ክርስቶፈር ፌርባንክ)

እሱ ከመጥፎ ጎኑ ባልሆንበት እሚሻለኝ አንድ ሰው ነው።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ምን? የእኔ መጥፎ ጎን ቢሆንሳ?

[ዘደላላ ሱቁን ከፈተ እና ጴጥሮስን ወደዉጭ ገፈተረው] 

ዘደላላ (ክርስቶፈር ፌርባንክ)

ደህና ሰንብት አቶ፣ ክዊል።

[በሩን ጴጥሮስ ፊት ላይ ከረቸመው] 

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

[በዘጋው ሱቅ በሩ በኩል አልፎ እየጮኸበት]

እንዴ፣ ቃል አስረን ነበር፣ ወንድም!

[መለስ ሲል ገሞራ በአቅራቢያው ሆና እየበላች ስታጤነው ተመለከተ] 

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ምን ተከሠተ?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ኧህ...ይህ ግለሰብእ የተስማማንውን ሰርዞ አሁን ወጣብኝ። እምጸየፈው አንድ ቢኖር ከወጥሃቀኛነት ዉጭ ያለ ሰውን ነው። ጴጥሮስ ክዊል። ሰዎች ሲጠሩኝ ኮከብ-ጌታ ነው እሚሉኝ።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

የክቡር ሰው ግርማ-ሞገስ ያለህ ነህ።

[በእጁ ላይ ጴጥሮስ ለጨዋታ ያክል ወደ ላይ ታች ሩሯን መወርወር ጀመረ] 

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ያው፣ ታዉቂያለሽ፣ ያንን እኔ እራሴው አልለውም። ሰዎች ስለእኔ ይሉታል፣ ሁል ጊዜ፣ ዳሩ ስለእራሴ ፈጽሞ የእማልናገረው የሆነ ነገር ነው።

[ገሞራ ከጴጥሮስ ሩሩን መነተፈች እና መልሳ ሆዱላይ መታችው እና እሮጠች። ጴጥሮስ የሆነ መግነጢሥአዊ ገመድ አስተኔ ወረወረባት ያም ገሞራ እግሮች ዙሪያ ተተብትቦ አሠናከላት። ከእግሮቿ ገመዱን ስታላቅቅ ጴጥሮስ ደረሰባት ግን ገሞራ ከራሷ ላይ መትታ እና ልትነድለው ችላ በቡጢም ትመታው ገባች። ሻሞላዋን ይዛም ልትበሳው ታዘጋጀው ጀመረ]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

[ገሞራ ልትበሳው እየሞከረች]

ዕቅዱ ይህ አልነበረም።

[ሮኬት በጀርባዋ ላይ ዘለለባት እና ዘረራት። ወደ ጴጥሮስ ልኮት እየከወነ]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

[ለጓደኛው ግሩት በመቻኮል]

ስልቻ ዉስጥ ክተተው። ስልቻ ዉስጥ ክተተው!

[ግሩት ስሮቹን ለጠጠ፦ ገሞራን በማደባሪያው ለማፈን]

አይ! እሷ አይደለም፣ እሱ!

ፆታዎችን አጥና፣ ሰውየው።

[እንኮኮ የወጣባት ሮኬትን ገሞራ ልትነክሰው ስትል እየተገታተረ]

ንክሻ? ያ ፍትሕአዊ አይደለም!

[ሮኬት ገሞራን ሲፋለም፣ ጴጥሮስ ይህን እድል ቀጥሮ ሩሩን ሞጨለፈ እና አስነካው]

[ሮኬት ገሞራን አመቻችቶ ለመያዝ እየተገዳደረ]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

አድርጊው ቀለል!

[ገሞራ ግሏን ከሮኬት ማስተው አሳካች እና ግሩት ጨምቆ ሲይዛት ሮኬትን ወደ ጎን ለመፈጥፈጥ አጎነችው ፣ ቀጥላ የብረት ቁስ አልማ ወደ ጴጥሮስ እጅ ወረወረች ያም ከእሚሮጥ ጴጥሮስ ሩር የጨበጠበትን መትቶት አስጣለው። ሮጣ ሩሩን ለቅማው ስትሮጥ፣ ጴጥሮስ በግሏ ላይ በመዝለል ተከመረ እና ዘረራት። ዳሩ ገሞራ ዳግም ጉልቤነቷ በለጠው እና ጴጥረለስን ለማጥቃት አመቻቸችው] 

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ቂል። ብትማር ይሻልህ ነበር።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አልማርም እኔ። ከችግሮቼ እንዳአንዱ።

[ጴጥሮስ ከእጇ ሩሩን ሞጨለፈ እና፣ ንዑስ ሮኬት አመንጣቂ (ላዉንቸር) በገሞራ ላይ አጣበቀ እና አነቃው፣ በእዛ ገሞራን ወደ ጎን አሽቀነጠረ። ነፃሆንኩ ሲል ግሩት የጴጥሮስን ራስቅል ስልቻውን ተጠቅሞ እስከ ወርችዎቹ ዘጋው]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

የምን አባ...

 [ግሩት ስልቻውን ቋጥሮ በጀርባው ለመሸከም አሽከርክሮ ጴጥሮስን ማዘል ጀመረ]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ማግጠጡን ተፋታ አንት ቂል። ባለሙያ ነህ ተብሎ ነው እሚገመተው።

[ልክ ወዲያው ገሞራ ሮኬትን ዳግ-ቀረበችአቸው]

እየቀለድሽኝ መሆን አለበት።

[ሮኬትን ወርውራ ፈጠፈጠች]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

እህ!

[ገሞራ ከግሩት ጋር ፍልሚያ ከወነች፣ እጆቹን ነሳችው። ልክ ጴጥሮስን ልትይዝ ስልቻውን ስትከፍት የተፈታ ጴጥሮስ ከመቅጽበት ሽጉጡን ተጠቅሞ ኤሌክትሪክ ተኩሶ አስያዛት እና እሮጠ። ሮኬት ሽጉጡን አዉጥቶ ወደ እሚሮጥ ጴጥሮስ አነጣጠረ]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ለትንንሾቹ ነገሮች ነው እምኖረው። ልክ ይሄ ምንያክል ይጎዳ ይሆን ለእንደ እሚለው።

[ጥይቱን የኤሌክትሪክ ኳስ ተኮሰበት ያም ጴጥሮስ ላይ የኤሌክትሪክ-ይዞታን አሰቃየ]

[ግሩትን ተመለከተ። እርሱም በመከፋት በገሞራ የተጎመዱ እና የወደቁ እጆቹ ላይ ዓይኖች ያንቀዋልል ነበር]

ታዲያስ። ማጎንቆል ነዋ፣ ትንሹ ሰው። 

ተመልሶ ያበቅላል፣ አንት ጥምብዝ ቂል።

[የወደቀ እጁን ጠለዘበት]

አልቃሻነቱን አቋርጥ። 

[በድንገት የኖቫ ጓዶች ደረሱ እና በበራሪዎች እንዳሉ እንዲንሳፈፉአቸው አደረጉ]

ኖቫ አሳሪ አብራሪ

እቃ ፹፱ፒ፲፫፣ መሳሪያህን ልቀቅ።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

አይ ቅዘን። ጥምብዝ ደደብዎች።

[ሮኬት በማቅማማት መሣሪያውን ለቀቀው] 

--

ኖቫ አሳሪ አብራሪ

በ ኖቫ ጓዶች ስልጣን፣ ሁላችሁም እናንተ እስር ዉስጥ ዉላችኋል...

[ጴጥሮስም አብሮ ታሠረ] 

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

[ዴይ ይዞት ለጴጥሮስ]

እሺ እንግዲህ። ና በል።

---

ኖቫ አሳሪ አብራሪ

የህይወት እና ንብረት ዉድመት አደጋ ስለመፍጠርአችሁ።

--

ኮርፕስማን ዴይ (ዮሐንሥ ሲ/ሬሊ)

እንዴ! ይሄ ኮከብ-ልዑል አይደል እንዴ!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ኮከብ-ጌታ።

ኮርፕስማን ዴይ (ዮሐንሥ ሲ/ሬሊ)

ይቅርታ። “ጌታ”።

ኮርፕስማን ዴይ (ዮሐንሥ ሲ/ሬሊ)

[አብሮት ጴጥሮስን እያሰረ በሌላ ጎኑ ለያዘው ጓደኛው]

ይህን ሰው አንድ ጊዜ ቀድሞ በእጅ አመል አስሬው ነበር። የ ምጢሬ መጠሪያ አጊንቷል።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ና እንጂ፣ ሰውየው። የ... የ ህግጣሽነት ስም እኮ ነው።

ኮርፕስማን ዴይ (ዮሐንሥ ሲ/ሬሊ)

ብቻ ፈታ በል፣ ጓዴ። ምስጢሬ ስም መያዝ ቀዝቃዛ እኮ ነው። ያን ያክል ኧው-አስብል (ዊርድ) አይደለም።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ፋሺስቶች።

[ሮኬት፣ ግሩት እና ሩህዋን የሳተች ገሞራ እንዲሁ ታሠሩ]

--------


ኖቫ አብይ ቅርንጫፍ

የዛንዳር ታጣቂ ኃይል


[ቀዳሚት ኖቫ የክሪ አምባሳደር ጋር ጥሪ በመከወን ላይ ነች]

ኖቫ ቀዳሚት (ግሌን ክሎስ)

በቤተክዋክብቱ (ጋላክሲ) ሁሉ የዛንዳርአዊያንን ኬላዎች ሮናን እያወደመ ነው። ያ የክሪ ወገንን ኢምንት ምላሽ ጥሪ ይጠራል ብዬ ባስብ ይሻለኝ አለ።

የክሪ አምባሳደር

የሰላም ስምምነትአቹን እኛ ፈርመን አለ፣ ኖቫ ቀዳሚት!

ምን እሚታከል  ደግሞ ፈለግአቹህ?

ኖቫ ቀዳሚት (ግሌን ክሎስ)

ቢያንስ ቢያንስ የሱን ድርጊቶች እናወግዝ አለን እሚል መግለጫ ከክሪ ልዑል-ግዛት። ታዳጊዎችን እያረደ ነው።ቤተሰቦችን።

የክሪ አምባሳደር

ያ የእናንተ ጉዳይ ነው። 

አሁን ፤ እምከታተላቸው ሌላ ጉዳዮች አሉብኝ። 

[ስልኩን አጠፋው]

ኖቫ ቀዳሚት (ግሌን ክሎስ)

ዋልጌ ሹም።

ዴናሪያን ሳል (ጴጥሮስ ሠራፊኖዊክስ)

ደህና፣ ትንሽ ጥሩ ወሬ። የሮናንን አንድ ወንዜልጅ አፈፍ ያደረግን ይመስል አለ።

[ዴይ ሁሉንም በየተራ ለሳል ያቀርብ እና ይዘረዝር ጀመረ] 

ኮርፕስማን ዴይ (ዮሐንሥ ሲ/ሬሊ)

ገሞራ። በቀዶጥገና የተሻሻለች እና ለነብስአማ መዋጊያነት የሠለጠነች። የቀዉሱ  ቲታን፣ ታኖስ፣ ማደጎ ሴትልጅ። ሠሞኑን፣ ታኖስ እሷን እና እህቷን ነቢውላ ለሮናን አበድሯቸው አለ ፤ ያም መርቶን እንድናምን ያደረገን ታኖስ እና ሮናን  አብረው እሚሠሩ እንደሆኑ ነው። 

እቃ ፹፱ፒ፲፫ እራሱን “ሮኬት” ብሎ እሚጠራ። የኢህግአዊ ዘረመልአዊ እና ስነአዉታርአዊ (ሳይበርኔቲክ) ሙከራዎች ዉጤት

ንዑስ ህይወት ቅጽ (ፎርም)።

[ግሩትን ልኮት አድርጎ]

ዴናሪያን ሳል (ጴጥሮስ ሠራፊኖዊክስ)

እንዴ ምን አይነት?

ኮርፕስማን ዴይ (ዮሐንሥ ሲ/ሬሊ)

ብለው ይጠሩት አለ “ግሩት”። ሰብእአማ (ሂውማኖይድ) ተክል ከሠሞኑን ወዲህ እየተዘዋወረ የነበረው እንደ የዕቃ ፹፱ፒ፲፫ ግልአዊ ቤት-ተክል ህዝባር ጡንቻ ሆኖ ነው።

[ጴጥሮስን ልኮት እያደረገ]

ጴጥሮስ እያሶን ክዊል፣ ከ ታራ። በዮንዱ ዑዶንታ እሚመራ ራቬጀሮቹ በእሚሠኝ የ ቅጥር-ተዋጊዎች (መርሰናሪስ) ማህበር ከታዳጊነት ጀምሮ ያደገ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

[ክዊል መሐል ጣቱን እንደ አንቀሳቃሽ አሽከርክሮ አመጣልአቸው እና ሰደበ]

እኔ አዘንኩ። ይህ አንቀሳቃሽ እንዴት እንደ እሚሠራ እኔ አላወቅኩም ነበር።

ዴናሪያን ሳል (ጴጥሮስ ሠራፊኖዊክስ)

ምን አይነት የቂ-ቀዳዳ መንጋዎች!

[ዴይ ፈገገ]

ሁሉንም አራቱን ወደ ኪልን አጓጉዙአቸው።


ኪልኑ

ልዕለደህንነት ቤተእስር


[እስረኛዎቹ ሲጓጓዙ ሆነ]


ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

[አብሮት ለእሚጓዙት ታሳሪዎች]

እንደ እምገምተው አብዛኞቸኀ ኖቫ ጓዶች ህግጋት ማክበር እሚሹ ናቸው፣ ግን እኒሆቹ እዚህ ያሉቱ፣ እነሱ በጣም ጨካኞች እና ሙሰኞች ናቸው።

ዳሩ፣ ኧረ፣ ያ የእኔ ቁብ አይደለም። እኔ እዚህ ብዙ ቆዪ አይደለሁም። ፳፪ ቤተእስረኛዎች አምልጫለሁ። ይሄኛው ምኑም አዲስ አይለይም።

አንተ እድለኛ ነህ እኒያ ሴታሴቶች እራስአቸውን አመጡ፣ ምክንያቱም ባይሆን ኖሮ፣ እኔ እና ግሩት ልክ አሁን ይሄኔ ወሮታውን እየሰበሰብን ነበር፣ እናም አንተ በዮንዱ እና እኒያ ራቬጀርስ ስቅላት-ሲደመር-ሰዉነት-መቆራረጥ (ድራውን ኤንድ ኳርተርድ) ላይ ትሆን ነበር።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ብዙ ጎበዞች በአመቶቹ ዉስጥ ሊገድሉኝ ሞካክረውኝ ነበር። እኔ በተክል እና አንደበትአማ እራኩን ልወድቅ የነበርኩ አይደለሁም።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ያዘው። ምንድር ነው አንድ ራኩን?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

 “አንድ ራኩን ምንድር ነው?” አንተ የሆንከው ነገር ነዋ፣ ነፈዝ።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ምንም ነገር እንደ እኔ አይደለም፣ በቀረ ከእኔ እራሴው።

[ወደ ህዋስዎችአቸው ሲጋዙ] 

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እና፣ ይህ ሩር የምር አብረቅራቂ አፎትማህደር አለው፣ የሙሴ ጽላት፣ የማልታ ፊልቆን፣ የሆነ ሰሞንኛሞቅታ ነው። ምንድር ነው?

ግሩት (ቪን ዲሰል)

እኔ ግሩት ነኝ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እና ምንይጠበስ? ሩሩ ምንድር ነው?

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ክብርየለሽ ለሆነ ቀማኛ ምንም ቃሎች የሉኝም።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

በጣም ከፍተኛ እና ሞገስአማ ነው ከዘርአጥፊ-ቀዉስ ሎሌ ሲመጣ።

[ገሞራ ወደ ሮኬት ተመለከተች]

አዎን፣ ማን መሆንሽን እኔ መንጥሬ አቅሽ አለሁ። ምንም የሆነ ማንም ማን እንደሆንሽ ያውቅ አለ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አዎ፣ እናውቅ አለን ማን እንደሆንሽ።

[ለግሩት]

 ማን ናት?

ግሩት (ቪን ዲዝል)

እኔ ግሩት ነኝ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እሺ፣ ያንን ብለህ አለህ።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ሩሩን ለሮናን እየለቀምኩለት አልነበረም። እየከዳሁት ነበር።

ለሦስትኛ ወገን ልሸጠው ቃል አስሬ ነበር።

ግሩት (ቪን ዲዝል)

እኔ ግሩት ነኝ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ደህና፣ ያ ለመጀመሪያዎቹ ፹፱ ጊዜዎች እንደነገርከኝ ልክ ማራኪ ነው።

እዚህ ““ለጋሡ ዛፍ” ጋር ያለው ችግር ምንድር ነው?

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ደህና፣ እንደ እኔ እና አንተ ደግ ማዉራቱን እሱ አያውቅበትም። እናም አንደበቱ (ቮካቡሊስቲክስ) በ “እኔ” እና “ግሩት” እና “ነኝ” የተገደበ ነው። በእዛ መደዳ ብቻ እና ብቻ። 

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ልንገርህ ምን መሠለህ፣ ያ ቶሎ ይሠለች አለ፣ በእዉነት ፈጥኖ።

[ጴጥሮስ ወክማኑ እና እራስስልክዎቹን (ሄድፎንስ) ለማጫወት አንድ ዘብ ጠቅ ሲያደርግበት ተመለከተ]

እንዴ! ያን አስቀምጥ።

[ወደ ነበረበት የዘቡ ክፍል ቶሎ ሹልክ ብሎ ገባ እና ስለንብረቱ ተገዳደረው]

እንዴ! አድምጠኝ፣ አንተ ትልቅ ሰማይአዊ ዲቃላ። እነዚያን እራስስልኮች አዉልቅአቸው፣ ያ የግሌ ነው።

[ዘቡ ጴጥሮስን በልምጭ ጢዝዝ አደረገው]

እነእዚያ በጊዜአዊነት እሚወረሱት ዉስጥ እሚገቡ ናቸው። ያ ቅረጽአጫውቴው እና ያ ማጫወቻ የእኔው ነው!

[ጴጥሮስ በቤተእስሩ ዘብ ተጨማሪ ኤሌትሪክ-ምት አገኘ]

አንድ ስሜት ዉስጥ ተሸነቀርኩ፣ ብሉ ስዌድ፣ ፲፻፸፫ (እኤአ.) ያ ሙዚቃ የእራሴው ነው።

[ተጨማሪ ንዝረት ተሰጠው እና ከቶ ተሸነፈ]

[ዘፈኑ በከፍታ ሲጫወት እንዲሁ ዘቡ ደግሞ ነደፈው።...]

[እንዲታጠቡ እና ልብስዎች እንደ ታሳሪዎች ለብሰው የእስርቤቱ ቁሳቁስዎችን እንዲሰጥአቸው ሆኖ አየን]

--------

[ቤተእስረኛዎቹ ዉስጥ]

እስረኛዎቹ

[ከእየአግጣጫው እስረኛዎቹ በአዲስ ገቢዎቹ እስረኛዎች ሲሲቀላቀሉአቸው ይጮኹ እና ይዝቱ ጀመር]

- አንተ ቀዳሚ ነህ! አንቺ ቀዳሚ!

- ነፍሠገዳይ! ቀድሜ አንቺ ጋር እመጣ አለሁ፣ ገሞራ!

- ሞተሽ አለ!

- አልጌ ነሽ! አልጌ ነሽ!

[ገሞራ የተለያዩ ቁሳቁሶች በሌላ እስረኞች ተወረወረባት]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

[ሮኬት አብረው ላሉት ሁሉ ስለድባቡ ማብራራቱን ቀጠለ]

ልክ እንደ አልኩት ነው። እዉቅና አካብታ አለች። ብዙ እስረኛዎች እዚህ ቤተሰቦቻቸውን በሮናን እና ቅጥር-ደብዳቢዎቹ  ያጡ ናቸው።

እስረኛዎቹ

[ገሞራን መስደቡን በተለየ ተያያዙት]

 -አንድቀን ትቆይ አለች፣ ቢበዛ።

 -ነብሠገዳይ!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ዘቦቹ ይጠብቋት አለ፣ አይደል?

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

እዚህ ያሉት ከመዉጣት ሊያቆሙን ነው። አይጨንቅአቸውም ዉስጥ እርስለእርስአችን በምናደርገው።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

[አስፈሪው ሁኔታን እንደ እማትሸነፍለት ልበሙሉነቷን ለማሳየት ፍራቻ ዉጣ ተናገረች]

መጭ ጊዜው የያዘአቸው ምንም ቅዠቶች ቢሆኑ ፣ ህልሞች ናቸው ከጀርባዬ ከተተወው ሲወዳደር።

ከእስረኛዎቹ አንዱ

[መግቢያ ሌላ በር ላይ ግድንግዱ ሰው ቆሞ በር በመዝጋት አዲሱን ቡድን አስቆመ]

አስፈሪ እስረኛ

አዲሡን ሥጋ ፈትሹት እማ! እኔ የጉናቪያኖችን ጀሊ ቅብትብት ነው እማደርግህ ከእዛ ወደ ከተማ እሄድ አለሁ... 

[ግሩት የጉልበተኛ እስረኛውን አፍንጫ በእንጨት ጣቶቹ ኮረኮረ እና በአየሩ እያሰቃየ አንሳፈፈው]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

[ለእስርቤቱ በሞላ በመጮኽ መናገር ጀመረ]

አንድነገር ግልጥ እናድርግ። ይሄ እዚህ ያለው፣ የእኛ ምርኮ ነው!

ልታገኙት ትፈልጉ አላችሁ፣ በእኛ በኩል ማለፍ አለብአችሁ! 

ወይም፣ የበለጠ እቅጩን፣ እኛ እናልፍብአቸሁ አለን!

[ግሩት አፍንጫውን ፎንኖበት ወፍራሙ ፍጥረት በወለሉ ተዘረረ እና አፍንጫውን ጨብጦ በስቃይ ጮኸ። ሁሉም እየተሻገሩት በመዝለል አልፈውት ሲሄዱ ጴጥሮስ ቀረ። ጴጥሮስን እሚነካ እንደእሚጎዳ ስላሳዩ እና ስላስፈራሩ አብሮነቱን አብልጦ ተመኘ]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

[ጣቱን በመጠቆም ጥለውት ገባ ወዳሉት ጓደኞቹ እያስመለከተ በድንገት በጉልበተኛው መዉደቅ ክዉ ላለው እስርቤት አስረዳ]

ከእነሱ ጋር ነኝ።

እስረኛዎቹ

እጠላሽ አለሁ። 

ሌላ እስረኛዎች

- ምንም ህዋስ ለረዥም ጊዜ እሚከልልሽ አይሆንም።

- ሞተሽ አለ!

- ሞታ አለች!

[ብዙዎቹ እየጮኹባት በቂም እየፈለጓት ወደ ህዋሷ ገብታ በሩን ስትዘጋ መጥተው መደብደብ ጀመሩ። እንደእሚገድሏት እየዛቱ በሂደት መበታተን ጀመሩ። በእሩቁ ተቀምጦ በታላቅ ጥላቻ እና ኩራት እእንዳለ ድራክስ አፍጥጦ ተመለከታት]

---

[ሁሉም ተኝቶ ሳለ ድንገት ገሞራ በሌሎቹ እስረኞች ትያዝአለች። ለሌላው የወቅቱ ዘብ አቅርበዋት ፈቃድ ሀሳብ በመጠየቅ ፊቱ ይዘዋት ቆሙ]

የእስረኛዎቹ ዘብ

[በታላቅ ንቀት ሆኖ]

ወደ ገላመታጠቢያው ዉሰዷት። ደሙን ለማጽዳት በእዚያ ቀላል ይሆን አለ።

[ይህን ሰምተው ገሞራን እያዳፉ እንደአነቋት ሊወስዷት ሲሉ ገሞራ በዘቡ ላይ ተቃዉሞ ለማሰማት ያቅሟን ትገታተር እና ድምጽ ታወጣ ጀመረ]

[ጴጥሮስ ከታሰሩት ሰዎች መሀል በወል ተደራርበው እና በእየፊናው ተቃቅፈው ከተኙት መሀል ሆኖ እንደነበረው በቅርበት የነበረውን የገሞራ ተቃውሞ ድምጽን ድምጽ ሰምቶ ነቃ]

[በመጠራጠር እየተከተለ ሊሄድ እሚያዳፏት ገሞራን ሊከተል ሲወጣ ሮኬትም ከሰመጠ እንቅል ነቅቶ የተኙትን ላለመቀስቀስ ቀስ አድርጎ ተጣራ]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ክዊል፣ የት ነው እምቴደው?

ክዊል! ክዊል!

እስረኛው

[ከጓደኞቹ ጋር እስረኛው ገሞራን ወደ ተፈቀደው ስፍራ ወስዶ ከግድግዳው አጣብቆ ይዞ ቢላዋ አዉጥቶ እያቀረበባት]

ገሞራ! ቤተክዋክብቱን ተፃርረሽ ለፈጸምሽአቸው ወንጀሎች ይህንን እንደ ሞት ቅጣት አድርገሽ እይው።

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

[ከጀርባ ድንገት ድራክስ መጥቶ እየቀረበ ማቋረጥ በቅጽበቱ መጨረሻ ላይ ከወነ]

ትደፍር አለህ?

ታውቁ አላችሁ ማን እንደ ሆንኩ፣ አይደል?

እስረኛው

[እርብትብት እያለ ዞር ብሎ ድራክስን በማክበር]

አንተማ ድራክስ ነህ።

ደምሳሹ።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

[ጴጥሮስ እየተከታተለ ወደ ደረሱበት በዝግታ ሲያዘግም ሮኬትም እየተከተለ ሊያስቆመው ሞከረ]

ክዊል!

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

[ለእስረኛው]

እና ይሄን ብለው ለምን እንደእሚጠሩኝ ታውቅ አለህ።

እስረኛው

የሮናንን ደርዘን ንዑሴዎችን (ሚኒየንስ) በድል ገድለህ አለህ።

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

[ቀረብ ብሎ ተቀላቀለአቸው]

ሮናን ገድሎብኝ አለ የኔን ሚስት፣ ኦቬቲ፣ እና ሴት ልጄን፣ ካማሪያ። በቆሙበት ነበር ያረዳቸው። እና ሣቀ።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ክዊል።

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

የሷ ነብስ ልትወስደው ያንተ አይደለም። ቤተሰቦቼን ገድሎ ነበር። ከእርሱ አንዷን በምላሹ እኔ ልገድል ይገባል።

እስረኛው

እንዴ አዎ፣ ድራክስ። ይኸው፣ እኔ...

[እስረኛው ቢላዋውን ለድራክስ አስረክቦ ገሞራንም ለቀቀለት]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

[ጴጥሮስ እየሰጋ መቅረቡን ቀጠለ። አብሮትም ሮኬት ለማስቆም መከታተሉን ቀጠለ]

ክዊል! ምን እያደረግህ ነው?

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

[ድንገት ገሞራ ክፍተቱን አሽከርነት ቀጥራ ከመቅጽበት በቢላዋአቸው ድራክስን አንገቱ ላይ አቅርባ ቀጥ አድርጋ አቆመችው እና የበላይነቱን ወሰደች]

እኔ ለሮናን ወይም ታኖስ ምንም ቤተሰብ አይደለሁም። እኔ እሱን በማስቆሙ ላይ ብቸኛው ተስፋህ ነኝ።

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

[ነፃነቷን አሳውቃ ገሞራ ቢላዋውን በትምምን ወደ መሬቱ ጣለች እና አንገቱን ከአደጋው ለቀቀችለት]

[ድራክስ ስለተተወ ሳይጨነቅ ወደ ግድግዳው መልሶ እያጣበቀ ጮኸባት]

እንስት፣ ቃልዎችሽ ለእኔ ፍቺአቸው ምንም ነው!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

[ቀርቦ በመቆም ተገልሎ ሲመለከት የነበረው ጴጥሮስ ይሄኔ ጣልቃ ገብቶ ለማስጣል ወደ ትርዒቱ ገብቶ ተቀላቀለ]

እንዴ! እንዴ፣ እንዴ፣ እንዴ! እንዴ!

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

[ጴጥሮስ ላይ ተበሳጨ]

ቅዘን።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ታውቅ አለህ፣ ሮናንን መግደል የአንተ አንድኛው ኢላማ ከሆነ፣ አይመስለኝም ይህ በምርጡ መንገድ እምቴድበት መንገድ እንደሆነ።

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

አንተ ይች ቅሬ ልትገድል ሙከራ ያደረገችብህ ወንድ አየደደለህምን?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ደህና፣ ማለቴ፣ ያን ለመሞከር እና እኔ ላይ ለማድረግ የመጀመሪያዋ ሴት ነች ማለት ይከብድ አለ። እይ፣

ይህ ከ ራጃክ  እጅግ-ቀዉጢ ሴት ነው።

በሹካ በሳችኝ።

በፀሐይ ጎህ ስለያትም አሎደደችውም። 

ይኸው፣ ልክ እዚህ ጋር ደግሞ፣ 

የክሪ ሴት መሠልቀጫዬን ቦትርፋ ልታወጣው ሞከረች።

ኖቫ ማህደር ዉስጥ ከእምትሠራ አስካቫሪአዊት ጋር ያዘችኝ

መረጃ ልቀበላት እየሞከርኩ ነው የነበረው። 

አስካቫሪአዊ አይተህ አታውቅም?

ገመዴ (ቴንታክልስ)  አሏቸው፣ እና ጥርስአቸው መርፌዎች ናቸው።

በእዛ ከምሬ ይመለከተኛል እምል ከመሠለህ፣ በቃ....አንተ አትጨነቅ።

ግን ነጥቡ ያዉልህ።

እሷ ሮናንን ከድታ አለች። 

ለሷ ይመጣላት አለ።

እና ያኔ እሱ ሲመጣ አንተ...

[ጴጥሮስ ሌባ ጣቱን በአንገቱ አሳለፈ]

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

ለምን ብዬ ነው አንገቱ ላይ ጣቴን እማሣርፈው?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ምን?

[ጴጥሮስ ግራ ተጋብቶ ሁሉንም ተመለከተ። ቆይቶ ተረዳው]

አይ፣ ምልክት ነው። ይሄ አንተ አንገቱን ስትሸረክትለት እሚያሳይ ምልክት ነው።

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

መሠልቀጫውን እኔ አልሸረክትም። አናቱን ቆርጬ ነው እማነሳው።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

የሆነ ሠውን አንተ ስትገድል እሚያሳይ ጠቅላላ አገላለጽ ነው።

[ለባለቢላዋው]

አንተ ይህን ሰምተህ አለ አይደል።

[ለሌላው]

አንተ ይህን አይተሃል፣ አይደል?

 [ጣት አንገት ላይ እያሻገረ አሳየአቸው]

 ያ ምን እንደሆነ ታውቅ አለህ አይደል።

እስረኛዎቹ

አዎ...

አዎ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

[ለድራክስ]

ሁሉም ሰው ያዉቀው አለ!

[ድራክስ ሊሞክር በእሚመስል መንገድ ወደ አንዱ ታሳሪ ለማረጋገጥ ተመለከተ]

እስረኛው

አይ ኧረ!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እኔ እምለው፣ እሷን በሂወት ልታቆያት ያስፈልግህ አለ። አንተ የሱን ስራ አትስራለት።

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

[ድራክስ አቅማምቶ ተስማማ]

[ለባለቢላዋው]

ቢላዋህን ወድጄው አለሁ። እኔ አቆየው አለሁ።

እስረኛው

ከሁሉ እምወድደው ቢላዋዬ ያ ነበር። 

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

[በመመለስ ላይ ሳሉ]

ስሚ! ኑሪ ወይም ሙቺ እኔ ያነሰ መጨነቅ እችል አለሁ። 

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

እና ግብዳውን ሰውዬ ለምን አስቆምክ?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ቀላል ነው! የኔን ሩር የት እንደምሸጠው አንቺ ታዉቂ አለሽ።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

እንዴት ነው እምንሸጠው እሱ እና እኛ አሁንም እዚህ ሆነን?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እዚህ፣ የኔ ጓደኛ ሮኬት፣ ፳፪ እስርቤቶች አምልጦ ነበር።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

እኛ እኖጣ አለን። እና ወደ ዮንዱ ቀጥ ብለን እናቀና አለን ያንተ ወሮታውን ለመልቀም።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ምን ያክል ነው ገዢሽ ለሩሬ ሊከፍልሽ ፈቃደኛ የነበረው?

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

አራት ቢሊየን አሃዶች። 

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ምን?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እንዴት ያለ ቅዘን!

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ያ ሩር ከታኖስ እና ሮናን ለማምለጥ እድሌ ነበር። አርነት ብታወጣን፣ ወደ ገዢው ቀጥታ እኔው አመራህ አለሁ እና ትርፉን በሦስትአችን መሀል አከፋፍለው አለሁ።

ግሩት (ቪን ዲዝል)

እኔ ግሩት ነኝ።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

እኛ አራትአችን። ለአደጋው ማንቀላፋት፣ ለገንዘቡ መንቃት፣ እንደወትሮው ጉደኛ!

--------


[በሮናን መርከብ ገጽማያ ተከፍቶ የታኖስ ታዛዥ በምስልስልኩ ልዉዉጥ ይቆጣ አለ]

ዘ አዘር (የታኖስ ታዛዡ)

ሮናን፣ ተከድተህ አለ።

ሮናን (ሊ ፔስ)

እኛ እምናውቀው እንደተማረከች ብቻ ነው። ገሞራ ሩሩን ገና ትለቅም ይሆን አለ።

ዘ አዘር (የታኖስ ታዛዡ)

የለም!

ኪልን ዉስጥ ያሉት የእኛ ምንጮች ገሞራ ለሩሩ የግሏን ዕቅዶች ይዛለት አለች ይላሉ።

ተመልከት፣ ከታኖስ ጋር ያለው ሽርክናህ አደጋ ላይ ወድቋል። ታኖስ ያንተን መቅረብ ይጠይቅ አለ።

አሁኑኑ!

--------


ሳንክቹዋሪ

የታኖስ እርስት (ዶሜይን)


ሮናን (ሊ ፔስ)

ከሙሉ አክብሮት ጋር፣ ታኖስ፣ ያንተ እንስት ልጅ ይህንን ዝርክርክ ሠራች፣ እና፣ ዳሩግን፣ እኔን እንድቀርብ ጠየቅህ። 

ዘ አዘር (የታኖስ ታዛዥ)

እኔ ብሆን ድምፄን ዝቅ አደርግ አለሁ፣ ከሣሹ።

ሮናን (ሊ ፔስ)

መጀመሪያ፣ ከሆነ ኋላቀር ጋር ፍልሚያ ተሸነፈች።

ዘ አዘር (የታኖስ ታዛዥ)

ታኖስ ገሞራን በአንተ ዕዝ ስር አስቀምጧል።

ሮናን (ሊ ፔስ)

ከእዚያም በኖቫ ጓዶች ታስራ ነበር።

ዘ አዘር (የታኖስ ታዛዥ)

እዚህ ለመምጣትህ እሚገባ እምታሳየው ሳትይዝ የቀረብክው አንተው ነህ።

ሮናን (ሊ ፔስ)

የአንተ ምንጮች እሚሉት እኛን ልትከዳን የነበረው ሁሌም እንደ ነበረ ነው!

ዘ አዘር (የታኖስ ታዛዥ)

ድምጸትህን ቀንስ! እኔ ያንተ ልሆን እምችለው...

[ሮናን ታዛዡን ኮስሚ-ሮድ አሽከርነት ገደለው]

ሮናን (ሊ ፔስ)

እኔ እምጠይቀው ይህን ጉዳይ ከምር እንድትወስደው ብቻ ነው።

ታኖስ (አሌክሲስ ዴኒስኦፍ)

[ከመንበሩ ጀርባውን መስጠቱን አቋርጦ ወደ ሮና ን መንበሩን ጭምር ዞረ]

ከምር የማልወስደው ብቸኛ ጉዳይ፣ ልጅ፣ አንተን ነው። ስነዉሳኔህ (ፖለቲክስ) ይሠለቸኛል። ነገረስራህ ሁሉ የጩጬ ማላዘን ነው። እና፣ ግንባርሥጋ እንደሆነው፣ ከሁሉ የእምወዳትን እንስት ልጄ፣ ገሞራን ባይተዋር አድርገህ አለህ። እኔ ቃሌን እማላጥፍ ነኝ፣ ክሪ፣ ከሆነ የኔን ሩር እምታቀርብልኝ። ግን፣ ሌጣ-እጅ ድጋሚ ወደ እኔ ተመለስ፣ እና በደምህ ፍኖተኮከቡን ነው እማጥበው።

ነቢውላ (ኬረን ጂላን)

[ከተቀመጠችበት እና የአንቀሳቃሽ እጇ ላይ ስትጎረጉር እና ስታድስ የነበረችው ነቢዉላ እጇን ማደሱን ትታው ተነስታ ቀረበች]

እናመሰግንህ አለን፣ አባ። ፍትህ ይመስል አለ።

[ለሮናን]

ይሄ የእማታሸንፈው አንድ ፍልሚ ነው። ወደ ኪልን እናምራ።

--------


[ኪልን ቤተእስሩ ዉስጥ]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

[መብል ድርጎ (ራሽን) ተቀብለው እየተቀመጡ ስለማምለጡ ሮኬት ያብራራ አለ]

እኛ ከእዚህ እምንወጣ ከሆነ፣ ወደ እዛ መመልከቻማማ መግባት ያስፈልገን አለ። እና ያንን ለማድረግ ጥቂት ነገሮች ሊያስፈልጉን ነው።

ዘብዎቹ የደህንነት አምባር ይለብሱ አለ፣ መግቢያ መዉጫዎችአቸውን ለመቆጣጠር። አንድ እፈልግ አለሁ።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ያን ለእኔ ተወው።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ያ ጓዴ፣ እዚያ።

[አንድ ቆማጣ በሰውሰራሽ አካልተኪ (ፕሮስቴቲክ) እግር እየታገዘ ድርጎውን ተሸክሞ ሲያልፍ እሱን ልኮት እያደረገ]

አካልተኪ እግሩን እፈልገው አለሁ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

የሱን እግር?

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

አዎን። የቀረ እሱን እንደእማልፈልግ እግዚእአብሔር ያውቀው አለ። ተመልከቱት እስኪ፣ ምኑ ይጠቅም አለ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ይሁን እሺ።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

እና በመጨረሻ፣ በእዚያ፣ ግድግዳው ላይ ጥቁር መለደፊያ (ፖናል) አለ። ተጣቃሽ ቢጫ ብርሃን። አያችሁት?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አዎን።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ከጀርባው አንድ ኳሪንክስ ቋቴ (ባትሪ) አለ። ሀምራአዊብጤ ሳጥን፣ አረንጓዴ ሽቦዎች። ወደ እዚያ መመልከቻማማ ለመግባት በእርግጠኛነት እፈልገው አለሁ።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ያንን እንደምናደርግ የታሠበው እንዴት ሆኖ ነው?

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ደህና፣ እንደእሚገመተው፣  እኒህ መላጣ-አካሎች ቆንጆ ነሽ አሉ። እና፣ ምንአልባት የሆነ ንግድ ብጤ ነገር ታመቻቺ ይሆን አላ።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

እያሾፍህ መሆን አለበት።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ኧረ፣ ከምር ጉምጉም አድምጬአለሁ ቆንጆ ሆነሽ እንዳገኙሽ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ተመልከቱ፣ ፳ ጫማዎች ወደ አየሩ ነው፣ እንዲሁም በጽኑ በእሚጠበቀው የቤተእስረኞቹ ማእከል ላይ ነው እሚገኘው። ወደ እዚያ ሳይታዩ ለመድረስ ፈጽሞ አይቻልም።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

አንድ ዕቅድ አለኝ፣ እና ያ እቅድ አንድ ጉደኛ ኳሪንክስ ቋቴ ይጠይቅ አለ፣ ስለእዚህ መላውን ፈይዱት! አሁን ወደ እዛ መመለስ እችል አለሁ?

[ግሩት ወደ ቋቴው ቀርቦ አካሉን በማርዘም ቀረበው]

አመሰግን አለሁ። አሁን፣ ይህ ተፈላጊ ነው። ልክ አንዴ ቋቴው እንደተላቀቀ፣ እያንዳንዱ ነገር ከ ድንገተኛጊዜ ዘረዘዴ (ሞድ) ጋር ይላተማል።

[ግሩት የቋቴውን ክዳን በእሚራወጡ ሰዎች መሀል ነቅሎ ወደ ጀርባው ዝምብሎ ሳይመለከት ወረወረው እና አንድ ድርጎ ወሳጅ እስረኛ አናትን መታ እና የተመታው ወደቀ]

እኛ አንዴ እንዳገኘንው፣ ፈጥነን መንቀሳቀስ አለብን፣ እና በእርግጠኝነት ያንን በመጨረሻ ነው ማግኘት ያለብአቹህ።

[ግሩት ቋቴውን ነቅሎ አወጣው። እስርቤቱ መጨለም እና የአደጋጊዜ ድምጽ በትልቅ ገሃድ ማጮኽ ጀመረ። ሮኬት እና ጓደኞቹ ግ ተመለከቱ። ቋቱን ለሮኬት ማቅረብ ሲጀምር ብዙ እስረኛዎች መራወጥ እና ወደ ህዋስዎችአቸው ለመደበቅ መክነፍ ጀመሩ]

ወይም፣ ቀድመን ልናገኘው እና ሊብቃቃ ይጠይቀን ይሆን አለ።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

[ጊዜ እና ሁኔታ ለማብቃቃት ብላ ለመሮጥ እየተዋከበች]

እኔ አምባሩን አገኝ አለሁ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

[ጴጥሮስም እየተቻኮለ]

እግር!

ዘብ

[ለግሩት]

እስረኛ፣ በቅጽበት መሳሪያውን ጣል እና ወደ ህዋስህ አፈግፍግ፣ ወይም ተኩስ እንከፍት አለን።

ግሩት (ቪን ዲዝል)

እኔ ግሩት ነኝ።

ዘብ

[ለታዛዦቹ ዘብዎች]

ተኩሱ!

[ለእስረኛው ሁሉ መልእክት]

ሁላችሁም እስረኛዎች ወደ መተኛ ሥፍራዎችአችሁ ተመለሡ።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

[ወደ ግሩት ቀርቦ]

አንተ ደደብ!

 [የግሩት ሰውነት ላይ ወጣ]

እንዴት ነው እነዚህን ነገሮች እምዋጋ እንደ ሆነ እምገመተው፣ ካለ ቁሶቼ?

ዘብ

አዉሬው ቁጥጥር ላይ ነው። በእኔ ዕዝ ተኩሱ! 

[በግሩት ደና ትከሻው ላይ የተንጠለጠለ ሮኬት ላይ ሲተኩሱ፣ ግሩት በሰውነቱ እየከለለ ሁለቱንም መከተ]

[የቤተእስሩን ተኳሽ የአንድ መደዳ ዘብዎች ድራክስ ደበደበ። በእነግሩት ከመተኮስ አስትቶአቸው ከረታ በኋላ፣ የአንድ ዘቡን መሣሪያ ይቀበል አለ። ለሮኬት ለመወርወር ተዘጋጅቶ]

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

አስደንጋጭ ትንሽ አዉሬ!

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

[ሮኬት ዞረለት። ድራክስ መሳሪያውን በአየሩ ወረወረለት። እረካ]

ዑፍ፣ እሠይ።

[በእሚተኩሱት ንዑሴዎች ይመልስ እና ሮኬት ይተኩስ ጀመረ ግሩትም ይከላከል ቀጠለ]

--------

[ጴጥሮስ በህዋሱ የሸሸ እና የተቀመጠ ባለትክ እግር ሰውየውን እያጨዋወተ]

እምትፈልገው ምንድነው?

--------

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

[ለዘቡ በእጁ ያለ መሳሪያውን ቢጣበቅም ልኮት እሰጠች]

ይህን እፈልገው አለሁ።

ዘቡ

መልካም እድል! ወደ ዉስጥ ሽቦ-ግንኙ ነው።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

የሆነ ነገር መላ እዘይድ አለሁ።

[በእግሯ እጁን ለመገንጠል ጉልበት ስታሳርፍ ጮኸ]

--------

[ጴጥሮስ ሰውሰራሽ እግሩን ይዞ ሲሮጥ በመሀል አንድ ዘብ ጥይት ደግኖ]

እግሩን ጣል! እግሩን ጣል። እና ወደ ህዋስህ ተመልሰህ ተንቀሳቀስ!

[ቀዝቀዝ ብሎ ቆየት አለ ጴጥሮስ። ከመቅጽበት የተደገነበትን መሳሪያ በዉሸት እግሩ መታ]

--------

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ሮኬት!

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

[ለግሩት]

ወደ መመልከቻማማው ተንቀሳቀስ!

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

[ጴጥሮስን ለመተኮስ የፈለገውን ንዑሴ ዘልሎ በመቀለብ እና መገነጣጠል አወደመ።]

አንተ! አንዷ አስካቫሪያአዊትን ያወጣሃት ወንድ!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

[በችኮላ ወደ ማማው እግሩን እንደምንም ተሸክሞ እየወጣ]

አንድ ጊዜ ነበር፣ ሰዉዬ።

--------

[መመልከቻማማ ዉስጥ ይደርሱ አለ]

የመመልከቻማማው ዘብ

መገኘት እሚችሉ ዘብዎችን ሁሉ እንፈልግ አለን ፣ በሙሉ ዉጊያ ትጥቅአቸው ሆነው... 

[ሁሉም አራቱም የማማው በር ላይ በኩራት ቆመው ነበረ። ዘቡ በመስጋት ሲመለከትአቸው ግሩት እጆች አርዝሞ በመለጠጥ አንስቶት በማውጣት ከግድግዳ አላተመው]

[መቆጣጠሪያው ላይ ተሰብስበው ሮኬት ነገሮቹን እና ቁልፎቹን እና ኤሌክትሪክ ገመድዎቹን መበጣጠስ እና ማገጣጠም ጀመረ]

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

[ለገሞራ]

ቆሻሻ ፍጠትሽን አንሺልኝ፣ እንስት።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

[ለእነጴጥሮስ]

ይኼኛው እዚህ ያለው ለምንድር ነው?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

የአንቺን አለቃ እስኪገድል ድረስ ከአንቺ ጎን እንደ እሚቆይ ቃል ገብተንለት አለ።

ምንጊዜም ቃልኪዳኖቼን እጠብቅ አለሁ፣ ከአልጠበኳቸው ለእሚገድሉኝ ጡንቸኛነት ላይ ለታሠሩ ማጅራትምት-ሠራተኛዎች የገባኋቸው ሲሆኑ።

 [ያመጣውን ሀሰተኛ እግር ለሮኬት እየሠጠ]

ይኸው እንካልህ!

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

[ሮኬት አሁንም ቁሳቁሶቹን እየነካካ በማስተካከል ሳለ]

ኡው! ስለእግሩ ስቀልድ ብቻ ነበር። እነዚህ ሁለት ነገሮችን ብቻ ነበር የፈለግኳቸው።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ምን?

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

አይ፣ ያስቃል ብዬ አስቤ ነበር። ያስቅ ነበር? ቆይ፣ እንጣጥ እያለ ሲረማመድ ምን ይመስል ነበር?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

፫፻፻፻ አሃዶች ማዘዋወር ነበረብኝ!

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ቅቅቅቅ...

[ሣቀ]

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

እንዴት ነው እምንወጣው?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ደህና፣ አንድ ዕቅድ አለው። አይደለም?

ወይስ ያም ሌላው የፈበረክው ነገር ነው?

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

[ቸኳይ ስራውን ተያየደዞ እንዳለ]

አንድ ዕቅድ አለኝ! አንድ ዕቅድ አለኝ!

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

ንዝንዝህን አራግፈው እና ከእዚህ አጨናናቂ መታፈግ ገላግለን።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አዎ፣ በእዛ ነገር ከእዚህ እሚራመደው ሙዳየቃሎች መስማማት አለብኝ።

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

ከቶ ደግመህ እኔን ሙዳየቃልዎች ብለህ እንዳትጠራኝ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ፈሊጥ እኮ ነው፣ ጓዴ።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

የእሱ ሰዎች ሙሉበሙሉ ጥሬ ናቸው። ፈሊጦች ከአናቱ ሽዉ ሊሉ ነው።

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

ምንም ከአናቴ ሽው አይልም። የኔ ደመነብስ እንቅስቃሴዬ (ሪፍሌክስ) ከፍተኛ ፈጣኖች ናቸው። እሞጨልፈው አለሁ።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

በቤተክዋክብቱ ታላላቅ ጅላጅሎች ተከብቤ መሞቴ ነው።

[የእስርቤቱ ዘብዎች መመልከቻማማውን ከበቡ እነእሱም ግድንግድ መሣሪያዎች በመሸከም ሆነው ነው]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እኒያ ትላልቅ ጠብመንጃዎች ናቸው።

የአመጽ ዘብ እራስ

[ለታዛዥ ዘብዎች]

በእኔ ዕዝ! ቁጥር አንድ!

[ከዘብዎች አንዱ መሳሪያውን ተኮሰው ያም የመመልከቻማማውን መስታወት መስኮት መታ]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ባለሹል ጥርስአማ፣ ለዕቅዶችህ ዝግጁ ነን።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ቆይ አንዴ!

የአመጽ ዘብ እራስ

ቁጥር ሁለት!

[ሌላ ዘብ መሳሪያውን ተኮሰ ያም የመመልከቻማማውን ሌላ ክፍል መታ]

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

[ወደ ሮኬት ልኮት እየሰጠ]

ይህን እንስሣ እኔ አስታውሰው አለሁ። እንደልጅነት፣ የመጥበሻ እሳት ነበልባል ላይ ጠብሰንአቸው ነበር። ሥጋዎችአቸው እጅጉን ይጣፍጥ ነበር።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

አጋዥ አይደለም!

የእስረኛዎቹ ዘብ

ቁጥር ሦስት!

[ሌላው መሳሪያውን ሲተኩስ ያም ሌላ መስታወት መስኮት ከመመልከቻማማው መታ፣ ትልቅ ቀዳዳ ተወ።]

ሁሉም ይተኩስ በእኔ ዕዝ! ሦስት! 

[ሮኬት እንደእሚችለው በመፍጠን ሊያድንአቸው ይሰራ አለ]

ሁለት!

አንድ!

[ልክ ያኔ ሮኬት የአበጃጀአቸው አዳዲስ መሳሪያዎች ሲያቀጣጥልአቸው እና ጨርሶ ሲገለገል ሆነ። ያም ስህበቱን በእስርቤቱ ስለሰረዘ ሁሉም የእስርቤቱ ነገር ደና ሰው በአየሩ መንሳፈፍ ጀመረ]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

[ሁኔታውን በማስተዋል ዝቅ ብላ ተመለከተች]

ሠውሰራሽ ስህበቱን አጠፋው፣ ሁሉም ሥፍራ ላይ ነገርግን እዚህ።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

አንድ ዕቅድ አለኝ ብዬ ነገርኩአችሁ።

[ሮኬት መመልከቻማማውን አናት አካል ከተጣበቀበት ከመሠረቱ ነቀለ። እና የደህንነት ሰቤ (ድሮይድ) ተገልግሎ መሠረቱን ከአጠቃ በኋላ ሰቤዎቹን ጀቶች ቀጥሮ በመመልከቻማማው አናት አጣበቀአቸው። እንደ ጎማ አድርገው ሰቤዎቹ አየሩን እየወነጨፉ የመመልከቻማማውን አናት በማብረር ከእስርቤቱ ሮኬት አወጣ]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

[ከመመልከቻማማው ዉስጥ ወደ ዉጭው ወጡ። ተከትለው እንዳይመጡ በዘብዎቹ ደግሞ ያስወጣአቸው በሩን ከረቸመ። ነገርግን መመልከቻማማው ወደቀ]

ያ እጅግ ቆንጆ ዕቅድ ነበር።

[ሮኬት ሌላ የለም በማለት እሚጠበቀውን ያክል ስለከወነ ትከሻውን በማንቀሳቀስ እራሱን ተከላከመ። ሁሉም የግልዮሽ እቃዎችአቸውን ለመልቀም ተበታተኑ፣ ጴጥሮስም ህዋመርከቡን አሠሰ]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

[እየጠቆመ]

አዎ! ያው ያውና። መርከቤን አግኙልኝ። ሚላኖው ነው።፣ ብርቱካንአማው እና ሰማይአዊው ጥጋቱ ጋር ያለው።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

[ወደልብስዎችአቸው በመቅረብ እየተቻኮለ በመለቃቀም]

ፖንቴን ወደኳስነት አጨመዳደውት አለ። ያ ብልግና ነው! ያንተውን እጥፍጥፍ አድርገውት አለ።

[ጴጥሮስ በፊናው እንዲሁ ግልዮሽአዊ እቃዎቹን በርብሮ አገኘ እና ሩሩን በእሚፈትሸው ቦርሳ ተመለከትን]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

[ገሞራም በቅርበት ሆና እየተመለከተችው]

ሩሩ እዚያ አለ። እንሂድ!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

[ጴጥሮስ መበርበሩን ቀጠለ፦ ወክማኑን ፍለጋ]

ቆይ፣ ቆይ፣ ቆይ።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ምን?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ያ ዲቃላ መልሶ አላስቀመጠውም ነበር።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ምን መልሶ አላስቀመጠም?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እንኪ!

[ጴጥሮስ ቦቦርሳውን አስረከባት]

ወደ መርከቡ ዉሰጂአቸው። እኔ ተመልሼ እመጣ ዘንድ ይሁን።

[ቶሎ እየተቻኮለ ሮጠ]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ሊሆንልህ እሚችለው እንዴት ነው…

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ብቻ ሚላኖውን በአቅራቢያ አንዣብቡት። ሂዱ። ሂዱ!

[ጴጥሮስ እስርቤት ዘብዎቹን አንድበአንድ መሳሪያውን ተገልግሎ አጠቃአቸው እና ወደቁ]

[አንዱን ዘብ እንዲሁ ተኮሰበት እና ወደቀ]

ዘቡ

ወይኔ! አንገቴ!

[ሲያልፈው ዳግ-ተኮሰበት።]

[በተመሳሳይ ጊዜ ሌላዎቹ ሚላኖውን ተጭነዉበት ለጉዞ ዝግጁ ነበሩ እና ልብአቸው እንዳይደረስብአቸው እየተንጠለጠለ ጴጥሮስን መጠበቅ ተያያዙ]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

[ለገሞራ]

ደህና። እንዴት ነው ሊደርስብን እሚችለው?

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

[እሷም በመናደድ እና መጨነቅ እንደሆነች]

ያንን መረጃ ከእኔ መጋራቱን ዉድቅ አድርጓል።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ደህና፣ ይህስ ኧረ ወዲያ፣ እንዲያ ከሆነ! እዚህ አካባቢ እኔ የሆነ መሞት እሚመኝ ወሮበላ አልጠብቅም። ሩሩን አጊንተሽ አለ፣ አይደለም?

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

አዎን።

[ገሞራ ጴጥሮስ ያስረከባትን ቦርሳ ድንገት ጠርጥራ ፈተሸች እና ሩሩ እንደእማይገኝ አወቀች።]

[ጴጥሮስ ሩሩን በእጁ ወደ ላይ ወደ ላይ እየወረወረው በመጫወት ሆኖ ወደ ወክማኑ ሰራቂ ዘብ ሊቀበል ሲሄድ ተመለከትንው። በአናቱ ጠቅልሎ ሲአደምጥ የነበረው ዘብ ደግሞ ሳይመለከተው ማድመጡን ቀጥሎ ነበር። ድንገት ደርሶበት ጴጥሮስ ሩሩን አሽከር አድርጎ በአናቱ ላይ ዘቡን ጠፈረው]

[ሚላኖው ላይ ስንመለስ]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

የእማንሄድ ከሆነ አሁን፣ ወደ ቅንጥብጣቢዎች እንፈነዳዳ አለን።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

አይሆንም! ከሩሩ ዉጭ አንወጣም።

[ልክ ሲከራከሩ ወዲያው ጴጥሮስን እየበረረ ድራክስ ሾፈተረ]

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

እንሆን!

[ወደ መርከቡ ጴጥሮስን ለመሳፈር እረዱት። ድራክስ በጴጴጥሮስ ጀግንነት ተደነቀ]

ይህስ መንፈስ አስመልክቶ አለ። ለሮናኑ ዐዉድማ ትጉህ ድጋፍ ይፈጥር ይሆን አለ፣ ጓደኛ፣ ምንድር ስትለቅም ነው የነበረው?

[ጴጥሮስ ወክማኑን አስረከበው እና አለፈ። ድራክስ የወክማኑን ምንነት ፈተሽ አደረገው]

አንተስ ጅልአንፎ ነህ!

[በሚላኖው ሲጓዙ፣ ጴጥሮስ ሮኬትን መርከቡን ሲፈታታ አገኘው]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አት፣ ጠምዛዥ ዘበ-ደን (ሬንጀር)! ምን እያደፈግህ ነው? መርከቤን አትፈታታ እኔን ሳትጠይቀኝ! አየህ፣ ይህ ምንድር ነው?

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ያንን አትንካ! ቦምብ ነው።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ቦምብ?

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

እናስ!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እና እንዲሁ እንዲቀመጥ ትተው አለህ?

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

በሣጥን ልጨምረው ነበር።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ሣጥኑ ምን ማድረግ ቻይ ሊሆን?

[ሮኬት አንድ ሣጥን ሳበ እና የተጠቀለለውን ሥጦታ አወጣ እርሱም ሳትሞት እናቱ ለጴጥሮስ ያስረከበችው ነበር]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ስለ ይኼኛውስ?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አአይ! እንዴ! ኧረ፣ ኧረ። ብቻውን ተወው።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ለምን? ምንድር ነው?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አፍክን ዝጋ።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

እህ!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ያ ምንድር ነው?

[ወደሌላ ሮኬት ከመርከቡ ጎትቶ ወደአወጣው ነገር እያመለከተ]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ያ እንኳ ነገሮች እጅግ በጣም ለከረሩ ጊዜ እሚሆን ነው። ወይም ጨረቃዎችን ለማፈንዳት ከፈለግክም እንዲሁ።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ማንም ጨረቃዎች አያፈነዳም።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ከሁሉ ነገር ደስታውን መምጠጥ ብቻ ትፈልጊአለሽ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

[ለገሞራ]

እና፣ ስሚ፣ የገዢሽን መተባበሪያአዊ ልፈልግ ነው።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

እየሄድን አለን በተገቢው አግጣጫ። ለአሁኑ።

[ገሞራ ሩሩን አነሣች]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

በህብረት እንድንሠራ ከፈለግሽ፣ ጥቂት የበለጠ ልታምኚኝ መሞከር ሳያስፈልግሽ አይቀርም።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

እና አንተ ምን ያክል እኔን ታምን አለህ?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

[ሩሩን ከእጇ መልሶ ተረከበ]

ብዙ ተጨማሪ አምንሽ ነበር ይህ ምን እንደነበር የነገርሽኝ ቢሆን ኖሮ። ምክንያቱም የሆነ አይነት መሣሪያ እንደሆነ እየገመትኩ ነው።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ያ ምን እንደሆነ እኔ አላውቅም።

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

[ጴጥሮስ ሩሩን መርከቡ ላይ አስቀመጠው እና ድራክስ አነሳው]

መሣሪያ ከሆነ በሮናን ላይ ልንጠቀመው ይገባን አለ።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

መልሠህ አስቀምጠው፣ አንት ሞኝ። ሁላችን እኛን ታወድመን አለህ።

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

ወይም አንቺን ብቻ፣ ሴቷ ነብሠገዳይ።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

አንድጊዜ እንድትኖር አደረግኩህ፣ ልዕልት!

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

እኔ ልዕልት አይደለሁም!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እንዴ! ማንም ማንንም እኔ መርከብ ዉስጥ አይገድልም! ገንዘቡን እስክንቀበል ድረስ ህብር ዉስጥ ሠምጠን አለ።

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

[ድራክስ ሩሩን ለጴጥሮስ አሽቀነጠረለት]

እኔ ገንዘብ ዉስጥ ምንም ጉጉት የለኝም።

[ጥሎአቸው ሄደ]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ታላቅ።

ያ ተጨማሪ ገንዘብ ለሦስትአችን ማለት ነው። 

ግሩት (ቪን ዲዝል)

[እሚቆጠር እንደሆነ ለማስታወቅ ድምጽ አሰማ]

እኔ ግሩት ነኝ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ለአራትአችን። አጋሮች።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

አንድ ስምምነት አለን፣ ዳሩ እኔ ከመሰሎችአችሁ ፈጽሞ አጋሮች አልሆንም። ለሸማቹ በመንገድአችን እንደገባን እነግረው አለሁ። እና ክዊል፣ መርከብህ፣ እድፋም ነው።

[ገሞራ ተለይታአቸው ዞራ በደረጃው ተፈናጥጣ ተጓዘች]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ምንም ሃሳቡ የላትም። ጥቁር መብራት ቢኖረኝ፣ ሥፍራው አንድ የ ጃክሰን ፖሎክ ስእል ይመስል ነበር።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ችግሮች አሉብህ፣ ክዊል።

--------

[ኪልን ቤተእስረኛዎች ዉስጥ ሮናን እና ኔቢውላ አንዱን እስርቤት ዘብ እያሰቃዩ ነው]

የአመጽ ዘብ እራስ

እምልአለሁ። የት እንደሄዱ አላውቅም! እኔ እምልአለሁ።

ነቢውላ (ኬረን ጂላን)

ወዴት እንዳቀኑ ቢያውቅ ኖሮ፣ አሁንድ ድረስ ይነግረን ነበር።

የአመጽ ዘብ እራስ

ታዲያስ።

ነቢውላ (ኬረን ጂላን)

ሮናን፣ ቤተእስረኛዎቹን ለመከላከል የኖቫ ጓዶች አንድ በራሪ ልከው አሉ።

ሮናን (ሊ ፔስ)

ደህና፣ ከሆነማ፣ ወደ እያንድአንዱ ጠርዝ ጥጋት ኔክሮክራፍቶች ላኪ። ሩሩን ፈልጊ። በምንም መንገድ፣ በየቱም ዋጋ።

ነቢውላ (ኬረን ጂላን)

እና ይህ ሥፍራ?

ሮናን (ሊ ፔስ)

ኖቫዎች ምን እያሠስን እንደሆነ ሊያውቁ አይችሉም። ይጸዳ!

[በዕዙ መሰረት ይገድሉአቸው ጀመረ]

--------

[ደላላው ሥፍራ ዉስጥ ዮንዱ ጉብኝት አድርጎ ጴጥሮስ ከሩሩ ጋር እንደአመለጠ ተገነዘበ]

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

እንደ እዚህኛው ያሉ ቆንጅዬ ጢኒኒጥ በገሮች አሉህ እንዴ? በእኔ መቆጣጠሪያ ኮንሶል (ማጫወቻ) ላይ ሁሉንም በአንድ ረድፍ ላጣብቅአቸው እወድድአለሁ።

ዘደላላ (ክርስቶፈር ፌርባንክ)

እያሾፍህ እንደሆነ ወይም ካልሆነ መናገር አልችልም።

የዮንዱ ታዛዥ

ሙሉኛ (ፉሊ) ከምር በመሆን ላይ ነው።

ዘደላላ (ክርስቶፈር ፌርባንክ)

በእዛ ጉዳይ ከሆነ፣ ላሳይህ እችል አለሁ... 

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

[ሣቀ]

ዳሩ ቀድመህ፣ ይህ ሩር ምን እንደሆነ ንገረኝ፣ እንዲሁም ሁሉ ሰው ለምን እጅግ ብዙ ስለእርሱ እንደእሚጨነቅለት። እና ትነግረኝ አለህ፣ እዚያ ዉጭ ማን ሊገዛ እንደ እሚሻው።

ዘደላላ (ክርስቶፈር ፌርባንክ)

አለቃዬ፣ የ ዉድዕቃዎች ማህበረሰቡ እንደሆነው...

[ዮንዱ አቋረጠው እና ዝባዝንኬኛ በመናገር ያፌዝበት ተያያዘ]

የዉድዕቃዎች ማህበረሰቡ እንደሆነው...

[ዮንዱ አሁንም አቋረጠው እና ዝባዝንኬኛ እያወራ አፌዘበት]

የተዋዳጆች ማህበር ነው...

[ዮንዱ አሁንም አቋረጠው እና ተጨማሪ ዝባዝንኬኛ እያወራ አፌዘበት]

የ ዉድዕቃዎች ማህበረሰቡ በጣም የተቀራረቡ ጓዶች (ተዋዳጆች) ማህበር ነው…

[ዮንዱ አቋረጠው እና ደግሞ ዝባዝንኬኛ አወራ ያም ክራግሊንን አሳቀው]

ሊሆን በእሚችል መልኩ የገዢዎቼን ምስጢርአዊነት ልከዳ አልችልም!

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

[ፈላፃውን አንሳፈፈ እና በደላላው ፊት ዙሪያ አንዣብቦት ዮንዱ አስፈራራው]

አሁን፣ ድጋሚ ይህ ያንተ ገዢ ማን ነው?


ሰብሳቢው መርከብ ዉስጥ


ታነሪል ቲቫን፣ እሚሰበስበው (ቤኒሲዮ ዴል ቶሮ)

ከሪና።

ከሪና (ኦፌሊያ ሎቪቦንድ)

[የመስታወት አካል መወልወል ደና መፈተግ ላይ ሆና ቀና አለች በፍራቻ]

አቤት፣ ጌቶች።

ታነሪል ቲቫን፣ እሚሰበስበው (ቤኒሲዮ ዴል ቶሮ)

ያንቺ ዘሮች፣ ክንዶች አሏቸው፣ የሏቸውም እንዴ?

ከሪና (ኦፌሊያ ሎቪቦንድ)

እኛ አለን፣ ጌቶች።

ታነሪል ቲቫን፣ እሚሰበስበው (ቤኒሲዮ ዴል ቶሮ)

ከሆነ ተጠቀሚያቸው። ላስከፋችኝ የመጨረሻዋ ደንገጡር ምን እንደገጠማት ላስታዉስሽ አይገባኝም። 

ይገባኝ አለ?

[ከሪና የቀደመቻት ደንገጡር ላይ ተመለከተች እርሷም ሰብሳቢው መርከብ አንድ መስታዋት ግድግዳዎች ዉስጥ የተቆለፋባትን ሆና ስታስተውላት አሰጋቻት]

 ቸብ፣ ቸብ። የእኛ እንግዳዎች ፈጥነው እዚህ ይደርሱ አሉ።

[ከሪና በፍራቻ ተፋጥና የመስታወቱን ህዋሶች ወደማጽዳት ገባች]


ሚላኖው ዉስጥ


ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

በንቅዓት ሁኑ! ወደ ዉስጥ እምንገባ የሆንን ነን።

[ሁሉም ተመለከቱ፦ ልክ ሲሰርጉ ወደ ምንሙሥፍራ እርሱም ታላቅ የተነጠለ አናት እሚመስል ነው]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ዎው!

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

ያ ምንድር ነው?

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ምንሙሥፍራ ነው እሚሠኘው። የጥንት ምህዋርአዊ (ሴለስቲያል) ፍጥረቶች የተቆረጠው አናት። ተጠንቅቀህ ነቃበል፣ ፊትጥርሶችአማው።

ከቶ ምንም አይነት ደንቦች የሉም እዚህ።

[ደቦው በምንሙስፍራ ጎዳናው ላይ ሲረማመዱ እንመለከት ዘንድ ሆነ]


ምንሙሥፍራ 

የማዕድን ማዉጫ ሠፈር


ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

መቶ አመቶች ቀደም፣ የቲቫን ቡድን ቅሉ ዉስጥ የነበረ ነፍስአማ (ኦርጋኒክ) ቁስ ለመቆፈር ሠራተኛዎች ላኩ።

አጥንት፣ ጭንቅላት ዘርፈህዋስ (ቲሹ)፣ የሠረሠር ፈሳሽ። ሁሉም ጥሬሃብቶች ናቸው፣ በቤተክዋክብቱ ጥቁር ገበያ ዉስጥ ሁሉ በከፍተኛ ዋጋ እሚገመቱ ናቸው። ለህግጣሾች ብቻ የተስማማ በጣም አደገኛ እና ኢህግአዊ ስራ ነው።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ደግ፣ ከአንድ የወንበዴዎች ፈለኬ ነው የመጣሁት። ቢሊ ህፃኑ፣ ቦኒ እና ሳይዴ፣ ዮሐንስ ስታሞስ። 

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

እሚመስለው ልጎበኝኘው እምወድደውን ሥፍራ ነው።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አዎን፣ ይሻልህ አለ።

[የህፃናት ጋጋታ ከበበአቸው]

የምንሙሥፍራ ልጆች

ይቅርታ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ኪስቦርሳዎችአችሁን ተጠንቀቁ።

የምንሙሥፍራ ልጆች

ማንኛዉም አሃድ ብትለግሱን ትችሉ ይሆን?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ከእዚህ ዉጭ ዉጡ።

[ታዳጊዋ አንድነሴት ወደ ግሩት ተራመደች፣ አበባ ከመዳፉ አሳበበላት፣ መዠረጠው እና ከመራመዱ ቀድሞ አበረከተላት]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

[ወደ መጠጥቤቱ እየተራመዱ]

ሸማችሽ በእዚህ ነውን?

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

የእርሱን እንደእራሴ እምንጠብቅ ነን።

ወጠምሻ የመጠጥቤት ዘብ

[አንድ ተጠቃሚ ገፍትሮ እያስወጣ]

ዉጣ ከእዚህ ወዲያ!

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

ይህ ክብር ጠባቂ ከባቢ አይደለም። እየጠበቅን ምን እንድናደርግ ትጠብቁ አላችሁ?

[ቀጠሮውን እየተጠባበቁ፣ ድራክስ፣ ሮኬት እና ግሩት ሰከሩ እና ቁማር ይወራረዱ ጀመረ]

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

አዎ! አዎ!

[እየተጫወተ]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ያሁ!

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

የኔ ኦርሎኒ አሸንፎ አለ፣ በሁሉ ነገሮች እንደእማሸንፈው ሁሉ!

አሁን፣ እነዚህን ተጨማሪ ፈሳሾች ወደ ሰዉነቶችአችን እንክተት።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

እብድ መጥፎ-ቅዘን ያሎነ የተናገርከው የመጀመሪያው ነገር ያ ነው!


[በተመሳሳይ ጊዜ ጴጥሮስ እና ገሞራ በመጠጥቤቱ ባልኮኒው ላይ ሆነው አሉ]


ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ሰው ሆይ! አታምኝም ምንያክል ለነዳጅ እንደእሚያስከፍሉ እዚህ። በእዚህ ሥራ ከምር ገንዘብ ልከስር እችል አለሁ።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

የኔ ድር እንድንጠብቅ እያቆየን ነው።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

የድርድር ፈጣንዘዴ (ታክቲክ) ብቻ ነው። እመኚኝ፣ ይህ የእኔ ልዩአዋቂነት ቦታ ነው። ያንቺው እንኳ ይበልጥ ያለው “መዉጋት፣ መዉጋት፣ እኒያ ብቻ ናቸው የኔ መደራደሪያዎች” ነገር ነው። 

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

[ገሞራ ሳቅ አለች]

አባቴ ዲፕሎማሲ ላይ አላተኮረም ነበር።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ታኖስ?

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

እሱ የኔ አባት አይደለም። ታኖስ የኔን እትብት-ከተማ ሲይዝ፣ ወላጆቼን ፊትለፊቴ ገደላቸው። በድብደባ አሠቃየኝ፣ ወደ መሣሪያነት ቀየረኝ። ሙሉ አንድ ፈለኬ ሊያወድም ለታኖስ ሲናገር፣ እኔ...እኔ አጠገቡ መቆም አልቻልኩም እና....

[የጴጥሮስ ወክማንን ቀበቶው ላይ አስተዋለች እና ሳበችው]

ለምህ ሂወትህን ለእዚህ ስትል አደጋ ላይ ትጥል አለህ?

[ወደ ድምጽአጫዋቹ እየጠቆመች]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እናቴ ናት ለእኔ ሰጠችው። እናቴ ስታድግ ያደመጠቻቸውን ተወዳጅ ሙዚቃዎች ሁሉንም ከእኔ ጋር መጋራት ትወድድ ነበር። እኔዉም ላይ ያ እሚኖር ሆነ፣ የነበርኩ ጊዜ....እለቱ...ታዉቂ አለሽ፣... ምድርን የለቀቅኩ ቀን።

[ጴጥሮስ ወክማኑን ከገሞራ ወሰደ እና በቀበቶው ላይ አስቀመጠው]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

በእርሱ ምንድነው እምታደርግበት?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ማድረግ? ምንም። ታደምጪው አለሽ። ወይም መደበስ ትችይ አለሽ።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

እኔ ተዋጊ ነኝ እንዲሁም ቅጥር ነብሠገዳይ። እምደንስ አይደለሁም።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ከምር? እኔ ፈለኬ ዉስጥ፣ አንድ አፈታሪክ አለ አንቺን ስለመሰሉ ህዝቦች። ፉትሉዝ ተብሎ ይጠራ አለ። እና ዉስጡ፣  ታላቅ ጀግና ኬቪን ቤከን የተባለ፣ መላ ከተማውን ቂጥ-ላይ ዱላ የሻጠ ህዝብ አስተማራቸው መደነስን። ያም ከአሉት ነገሮች ሁሉ ታላቁ የሆነው ነው።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ማን ነው ቂጦችአቸው ላይ ዱላዎቹን የሻጠው?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ምን? አይ፣ ያ እኮ ብቻ...

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

በጣም ጭካኔ ነው።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ሰዎች እሚጠቀሙት (የጨፈገጉ ለማለት) ሐረግ-ፈሊጥ ነው።

[ጴጥሮስ የወክማኑን እራስስልኮች በገሞራው አናት አኖረ ፣ ያም ሙዚቃውን ታደምጥ ዘንድ ሆነ፣ ለቅጽበት ከአደመጠች በኋላ በመጮኽ ተናገረች]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

አስደሳች ነው!

[ገሞራ ስታደምጥ ሳለች ጴጥሮስ ሊስማት አዘመመ ወዲያውም በአንገቱ ቢላዋዋን አኖረች] 

አይሆንም! 

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ኦ! ኧረ ከቶ ምንድን ነው?

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ማን እንደሆንክ አዉቅህ አለሁ፣ ጴጥሮስ ክዊል! እና ያንተ... ያንተ የዳሌ ጥንቆላ እዚህ ያጋድመኝ ዘንድ ቅዠታም ባይተዋር የሆንኩ አይደለሁም።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ያ እዚህ እየተከሰተ ያለው ነገር አይደለም።

[ገሞራ አገቱን ስታተርፍለት፣ ጴጥሮስ ድራክስ፣ ሮኬግ እና ግሩት እየተደባደቡ መጠጥቤቱ ዉስጥ አስተዋለ]

አይሆንም።

[ጴጥሮስ እና ገሞራ መጠጥቤቱን ገቡበት እና ድራክስ፣ ሮኬት እና ግሩትን ለማስቆም ሞከሩ። ገሞራ ከግሩት ላይ ድራክስን ጎተተች]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

አቁሙት!

[ሮኬት መሳሪያውን ወደ ድራክስ ላይ አነጣጠረ እና ሊተኩስበት ሲዳዳ ጴጥሮስ ጣልቃ ገባ]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ምን እያደረግህ ነው?

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

ይሄ መለስተኛ-አዉሬ (ቨርሚን) ምንም ስለእማያውቅአቸው ጉዳዮች ይናገር አለ!

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ያ ሃቅ ነው!

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

ምንም ክብረት የለውም!

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ያም ቢሆን ሃቅ ነው!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ቆይ አንዴ! ቆይ አንዴ!

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

መለስተኛ-አዉሬ እያልክ ጥራኝ፣ ጠጣሩ ሰዉዬ! አንተም ብቶን ልክ እንደሌሎቹ ልትስቅብኝ ብቻ ነው እምትፈልገው።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ሮኬት፣ ሰክረህ አለ። እሺ? ማንም አንተ ላይ እየሳቀ አይደለም።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

እኔ የሆንኩ እማልረባ ነገር እንደሆንኩ ነው እሱ እሚያስበው! እንዲያ ያስብ አለ!

ደግ! እኔ እንድፈበረክ አልጠየኩኝም! ግንጥልጥል እንድደረግ፣ እና ተመልሼ እንድገጣጠም፣ ድጋሚ እና ድጋሚ፣ እና ወደ ሆነ አንድ...አንድ ትንሽ አዉሬ እንድቀየር አልጠየኩም!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ሮኬት፣ ማንም አንተን አዉሬ ብሎ አልጠራህም።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

እሱ  “መለስተኛ-አዉሬ” ብሎ ጠርቶኝ አለ! እሷ “ፊትጥርስአማ” ብላ ጠርታኝ አለ! እስኪ ጉደኛ ፊቶችአቹህ ላይ መሣቅ ትችሉ እንደሁ ከአምስት ወይ ስድስት ጥሩ ተኩሶች ጀርባ እንመልከተው!

[ሮኬት ወደ ድራክስ መሳሪያውን ሲደግንበት ዳግመኛ ጴጥሮስ በፊቱ ቆመ]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አይ፣ አይ፣ አይ! አራት ቢሊየን አሃዶች! ሮኬት! ና እንጂ፣ ሰዉየው! እንዴ! ለአንድ ተጨማሪ ቀፋፋ ምሽት ምጠጠው ከእዛም ሃብታም ነህ።

[ሮኬት ለቅጽበት አመነታ። ከእዛ መሳሪያውን ዝግ አደረገ]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ደህና። ዳሩ፣ ቃል ግን አልሰጥም፣ ይሄ ሁሉ ነገር ሲያበቃ፣ እያንድአንዳቹህ ያላችሁትን ቆሻሾች እስክታልቁ እንደእማልገድልአቹህ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አየህ? ልክ እቅጩን ከማንአችሁም የትኛቹህም ምንም ጓደኛ ለምን እንደሌላችሁ! አምስት ሰከንዶች የሆነ ሰውን ከመገናኘትአችሁ በኋላ፣ ወዲያው ልትገድሉአቸው እየሞከራችሁ ነው!

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

ኩርማን ጥጋቱን ከቤተክዋክብቱ ተጉዘን ያለን ነን። እና ሮናን ሙት ወደመሆኑ ምንም አልተቀራረበም።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

[ድራክስ ዞሮ ንዴት እንደላሰ ሆኖ አቀና]

ድራክስ!

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ተወው ይሂድ። አንፈልገውም።

[ልክ ያኔ የሰብሳቢው ረዳት፣ ከሪና፣ ወደ መጠጥ ገባች]

ከሪና (ኦፌሊያ ሎቪቦንድ)

እመቤቴ ገሞራ። ወደ እኔ ጌቶች አሻግርሽ ዘንድ እኔ በእዚህ ነኝ።

[ከሪና ወደ ሰብሳቢው መርከብ አጀበችአቸው]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

[ቤተመዘገቢያ (አርካይቭ) ዉስጥ በነብስ ያሉ መዛግብቶችን ተመለከተ]

እሺህ፣ ይህ ከቶ አስጨናቂ አደለም!

ከሪና (ኦፌሊያ ሎቪቦንድ)

የቤተክዋክብቱን ትልቁ የቤተአንስሳዎች (ፋዉና) ቅርሳቅርሶች፣ እና የባህሪዎች ሁሉ ዘረፍጥረቶች (ስፒሺስ) በቤትነት ይዘንአለ

[ወደ ሰብሳቢው ትልቅ ክፍል በእዚያ ሲጠብቅአቸው ወደነበረበት አስገባችአቸው]

ለእናንተ አቀርብላችሁ ዘንድ አለሁ፣ ታነሊር ቲቫን፣ ሠብሳቢውን።

ታነሪል ቲቫን፣ እሚሰበስበው (ቤኒሲዮ ዴል ቶሮ)

[ገሞራ እና ሰብሳቢው ወደ እርስእርስአቸው አቀኑ]

እዉይ፣ የኔ ዉድ ገሞራ። በዓይነሥጋ መገናኘቱ እንዴት ድንቅ ነው።

[ሰብሳቢው እጇን ሳመ]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

መደበኛነቶቹን እንዝለላቸው፣ ቲቫን። የተወያየንበትን ይዘንው አለን። 

ታነሪል ቲቫን፣ እሚሰበስበው (ቤኒሲዮ ዴል ቶሮ)

[ግሩትን ተመለከተ]

ምንድር ነው ይህ ዛፍ?

ግሩት (ቪን ዲዝል)

እኔ ግሩት ነኝ።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

እኔ አንድ ግሩት እገናኝአለሁ ብዬ አስቤ አላውቅም ነበር።

ታነሪል ቲቫን፣ እሚሰበስበው (ቤኒሲዮ ዴል ቶሮ)

አለቃ... 

[ቀረብ አለው ግሩት]

አሁን እንድከፍልህ ልትፈቅድልኝ ይገባህ ዘንድ አለ ፣ ስትሞት ሙትአካልህን ባለቤት እንድሆነው። በሞትህ ቅጽበት ነው፣ በእርግጥ።

ግሩት (ቪን ዲዝል)

እኔ ግሩት ነኝ።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ለምን ወደ ጉደኛ ወንበር እንዲቀይርህ ብለህ ነው?

ታነሪል ቲቫን፣ እሚሰበስበው (ቤኒሲዮ ዴል ቶሮ)

[ለግሩት]

ያንተ ለማዳ እንስሳህ ነውን?

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

የእርሱ ምን?

[ሮኬት መሳሪያውን ለመደገን ተያያዘ እና ሰብሳቢው ቂቂታ አሰማ፣ ገሞራ ጣልቃ እራሷን አገባች]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ቲቫን። በቤተክዋክብቱ ዙሪያ ኩርማን መንገዱን አቋርጠን ነበር፣ ይህን ሩር ለመልቀም።

ታነሪል ቲቫን፣ እሚሰበስበው (ቤኒሲዮ ዴል ቶሮ)

በጣም ደህና፣ እንዲያ ከሆነ። እንመልከተው ምን እንዳቀረብአችሁ።

[ገሞራ ጴጥሮስን ተመለከተች፣ እና እሱ ከቦርሳው ሩሩን አወጣ እና በድንገት አሟለጨው መልሶ ቀለበው]

[በወቅቱ ዙሪያ፣ የሰከረ ድራክስ ጥሪ እየከወነ አንድ ሰው በድንኳን ዉስጥ ተመለከተ]

--------

 ድምፀመስኮት (ራዲዮ) ሠው

ሦስት ኳሪንክስ ቋቴዎች፣ ሰባት የኮታቲ ፍሬ አፎቶች።

አአይ፣ ምንም አፎት የለም። ባለፈው ጊዜ፣ የላካችሁልኝ ጊዜ...

[በቅጽበት ድራክስ ከች ብሎ ከጀርባው ቆመ እና ቢላዋ መሰለወቀጫው ላይ አሳረፈበት]

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

[አገተው እና]

አንድ መልዕክት ብታሻግርልኝ ይገባህ አለ።

--------

[ሰብሳቢው ጋር እና ደቦው ጋር ተመለስን]

ታነሪል ቲቫን፣ እሚሰበስበው (ቤኒሲዮ ዴል ቶሮ)

ውይ፣ የኔ አዲስ ጓደኛዎች። ከስነፍጥረት እራሱ ቀድሞ፣ ስድስት ነጠላአዊያን (ሲንጉላሪቲስ) ነበሩ።

[መሳሪያ ተጠቅሞ ሩሩን ከቁልፉ ከፈተው እና ኁልቆመሣፍርት ድንጋዩን ለእይታ ፈለቀቀው]

ከእዛ ህዋው ወደ ኑባሬነት ፈነዳ፣ እና የእዚህ ስርአትዎች እርዝራዥ ወደ ተቀረጹ ክብ አካሉ ተሠበሰቡ። ኁልቆመሣፍርት ድንጋይዎች። እኒህ ድንጋይዎች፣ እሚመስለው፣ ያልተለመደ ጥንካሬ ባሏቸው ፍጥረቶች ብቻ እሚነካካ ነው።

ንጸሩ!

[ትልልቅ ፍጥረቶች ኁልቆመሣፍርት ድንጋዩን እንደመሳሪያ ሲጠቀሙ በገጽማያ ላይ አስመለከተአቸው]

የነዚህ ተሸካሚዎች ድንጋዩን በመጠቀም አንድ ሙሉ ስልጣኔን እንዳንድ ማሣ ስንዴ ሊያጭዱ እሚችሉ ናቸው።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

[ቀጣዩ ገጽማያ ምስል ፈለኬዎችን ሲያጠፉበት ይህን ድንጋይ የያዙትን እኒያን ባለልዩጉልበት ሰዎች አስመለከተ]

ትንሽዬ ሽንት ከእኔ እየወጣኝ ነው አሁንኑ።

ታነሪል ቲቫን፣ እሚሰበስበው (ቤኒሲዮ ዴል ቶሮ)

አንዴ፣ ለቅጽበቶች... አንድ ቡድኖች አቅሙን በመሀከልአቸው መጋራት ችለው ነበር። ነገርግን፣ እነእርሱ እራሥአቸው እንኳ ወዲያው? በእራሱ ወድመው ነበር።

[ምስሉ እነዚያን ቡድኖች የድንጋዩን ጉልበት ሲጋሩ ግን መቻል አቅቶአቸው ሲወድሙ አስመለከተ]

[ሩሩ ተከፈተ እና ኁልቆመሣፍርት ድንይ አስነጸረ። ሰብሳበከው ተገረመበት]

ዉብ!

ከፉክክር የራቀ!

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ምናምን ምናምን ምናምን።

እኛ ሁልአችንም በጣም ተማርከን አለ፣ ነጬ!

ነገርግን እንዲከፈለን እንወድድ አአለን።

ታነሪል ቲቫን፣ እሚሰበስበው (ቤኒሲዮ ዴል ቶሮ)

እንዴት እንዲከፈልህ ትወድድ አለህ?

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ምን ታስብ አለህ፣ ቅንጡው ሰውዬ? አሃዶች!

ታነሪል ቲቫን፣ እሚሰበስበው (ቤኒሲዮ ዴል ቶሮ)

በጣም ጥሩ፣ እንዲያ ከሆነ።

[ሰብሳቢው ገንዘቡን ሊያገኝ ሲያዘግም ከሪና፣ በኁልቆመሣፍርቱ ድንጋይ ተማርካቀረበችው]

ከሪና!

ወደኋላሽ ተመለሽ!!

 ከሪና (ኦፌሊያ ሎቪቦንድ)

[ወደድንጋዩ በድፍረት ቀረበችው]

ከእንግዲህ ወዲያ የአንተ ባሪያ አልሆንም!

ታነሪል ቲቫን፣ እሚሰበስበው (ቤኒሲዮ ዴል ቶሮ)

አይሆንም!

[ከሪና ደርሳ የሩር ፍሬውን ጨበጠች እና የቲቫን ሥፍራ እንዲፈነዳ መነሾ ሆነች። ያም ግሏን አወደማት በተጨማሪም የሰብሳቢውን ቤተመመዝገቢያ። ግሩት ሮኬትን አፈፍ አድርጎ ከስፍራው ወጣ ልክ ሲፈነዳ ፤ ጴጥሮስ እና ገሞራ ከጠረጴዛው ስር ወጡ እና ዉድመቱን ተመለከቱ]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ኧረ ምንድ...

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

[ገሞራ ሩሩን ብድግ አድርጋ መልሳ በመዝጋት ከረቸመች እና ኁልቆመሣፍርት ድንጋዩን አሰረችበት።

[ልክ የሰብሳቢውን በፍንዳታ የወደመ ሥፍራ ትተው ሲወጡ]

ምንም ይሁን ምን ሩሩ ዉስጥ የነበረው እንዴት ነው ቲቫን ይሸከመው አለ ብዬ ያሰብኩት?

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ስለምን እስካሁን ያንን ይዘሽው አለሽ?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ምን ማድረግ አለብን፣ እዛ ዉስጥ እንተወው?

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ቦርሳሽ ዉስጥ አሁን ድረስ እንደያዝሽው ማመን ያቅተኝ አለ!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ያ ቦርሳ አይደለም፣ ሻንጣ ነው!

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ይህንን ወደ ኖቫ ጓዶች ልናመጣው ይገባን ዘንድ ነው። ሊሸከሙት እሚችሉበት ዕድል አለ።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

እየቀለድከኝ ነው? በኖቫ ጓዶች ተፈላጊዎች ነን። ለሮናን በቃ አስረክቡት።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እና በቤተክዋክብቱን እንዲያወድመው?

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ምንድን ነህ፣ ከመሬት ተነስተህ፣ የሆነ ፃድቅ?

ቤተክዋክብቱ ላንተ ምን አድርጎልህ እሚያውቅ ነው? ለምን ታድነው ዘንድ መፈለግን አደረግህ?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ምክንያቱም፣ ዉስጡ ከእሚኖሩ አንዱ መሀይምዎች አንዱ እኔው ነኝ!

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ጴጥሮስ፣ እኔን አድምጥ።

በሮናን መዳፎች ድንጋዩ እንዲወድቅ መፍቀድ የለብንም።

ወደ አንተ መርከብ መመለስ አለብን፣ እንዲሁም ለ ኖቫዎች ልናደርሰው ይገባን ዘንድ ነው።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ትክክል፣ ትክክል፣ እሺ። እንደእማስበው አንቺ ትክክል ነሽ።

ወይ ደግሞ ሊያስረን እሚችል ላልሆነ፣ ለእጅግ ብዙ ገንዘብ ከልቡ ምርጥ ለሆነ ልንሰጠው እንችልም አለን። በሁለትአችሁ የነበሩ የእይታ ነጥብዎች መሀል በጣም ምርጥ ሚዛን ይመስለኝ አለ።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

አንተ ቀላል ሰው ነሀ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እኔ...

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና) 

 ክብረቢስ። እምነትየለሽ!

[ገሞራ ዞር አለች እና ራመድ ብላ ሮናን እና የእሱ ሠራዊት በመርከብዎች ሲመጡ ተመለከተች]

ወይኔ ጉድ!

 ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

በመጨረሻ! ጠላቴን ብገናኘው እና ባወድመው ይሻለኝ ሆነ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ለሮናንን ጥሪ አደረግህ?

[ልክ የሮናን መርከብዎች ሲያርፉ ዮንዱ እና ሰዎቹ በጎን ተከሰቱ]

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

ክዊል! እንዳትንቀሳቀስ፣ ልጅ!

[ገሞራ እና ጴጥሮስ ማምለጡን ተያያዙት]

እንዳትንቀሳቀስ! እስኪ ከጎዳናዬ ዘወር!

[ዮንዱ ማሳደዱን ጀመረ፣ በእዛው ጊዜ ዙሪያ ሮናን ከመርከቡ ወረደ፣ ድራክስም ቢላዋዎቹን አዉለብልቦ ይጠባበቀው ዘንድ አደረገ]

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

ሮናን ከሳሹ!

ሮናን (ሊ ፔስ)

መልእክቱን ያሰራጨህው አንተ ነህን?

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

አንተ ሚሽቴን ገደልህ። አንተ ሴት ልጄን ገደልህ!

[ገሞራ፣ ሮኬት፣ እና ጴጥሮስ ትንንሽ ማዕድኖች መቆፈሪያ ጎሬዎቹን አገኙ። ሦስቱም ተሳፈሩ]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

[ለሮኬት]

እኔ ነገርኩህ፣ ላንተ አይበቃህም። አሁን፣ እዚሁ ጠብቅ። እመለስ አለሁ!

[ነቢውላ ሦስቱን መቆፈሪያ ጎሬዎች በበረሩ ጊዜ ብዙ ሳያመልጡ ገና ተመለከተችአቸው]

ነቢውላ (ኬረን ጂላን)

ገሞራ ናት። ከሩሩ ጋር ማምለጥ ላይ ናት።

[ነቢውላ ወደ መርከብአቸው ተመለሰች እና ተሳፈረች። ሮናን ዞሮ ሊቀላቀላት ተራመደ]

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

አይሆንም።

[ድራክስ ወደ ሮናን ሮጠ ይህን በቢላዋዎቹ ሊያጠቃው አደረገ ዳሩ ሮናን በቀላል ዝቅታ ሽል አለው]

ሮናን (ሊ ፔስ)

ነቢውላ፣ ሩሩን ልቀሚ!

[ሮናን ድራክስ ጋር ፍልሚያ እየያዘ። ነቢውላ ሦስቱን ማሳደዱን ጀመረች።]

--------

ነቢውላ (ኬረን ጂላን)

ድንጋዩ ከሁሉ በራቀው ጎሬ ዉስጥ ነው።

ፈጥፍጡት!

[ኔቡላ የገሞራን መርከብ ማባረር ጀመረች፣ በጊዜው ዙሪያ ድራክስ መፋለሙን ከሮናን ዘንድ ተያያዘው፣ ኔቢውላ ገሞራን ስታሳድድ ጴጥሮስ መርከቡን ወደ ሮኬቱ አቀረበው]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ሮኬት፣ አግድአቸው ገሞራ ወደ ሚላኖው እስክትደርስ ድረስ።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

እንዴት? በእነዚህ ነገሮች ምንም መሳሪያዎች እምናገኝ አይደለንም።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እነእዚህ ጎሬዎች የማምረቻ ደረጃ ናቸው። ኢመደምሠስ ላይ የቀረቡ ናቸው ማለት ይቻል አለ።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ከኔክሮብላስትዎቹ ሲፃረሩ ግን አይደለም፣ ኢተደምሳሽ አይደሉም።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ያን አይደለም እያልኩኝ ያለሁት።

--------

[ሮኬት ጎሬውን ወደ እሚያሳድዱአቸው ሁለት መርከብዎች ወሰደ፣ ወደ እያንድአንዱ ወስዶ አጋጨ እና ደመሰሰአቸው። ከእዚያ ሌላ ቀረብ ብሎ በመምጣት ተኩስ ሲልክበት ሮኬት በቀጥታ በርሮ ተጋጨው ያም አጋየ እና ከሰከሰው። ጴጥሮስ ከእሚያሳድዱት አንዱን መርከብጠለፋ ከወነበት]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ያንተን መጋለቢያ ልበደር።

[ሮናን እና ድራክስ ዐዉደ ፍልሚያአቸውን ቀጠሉ እንዲሁም ድራክስ ተጠብጥቦ አንገቱን በሮናን ተጨምቆ ተለቀመበት]

--------

ሮናን (ሊ ፔስ)

ቤተሰቦችህን መግደሌ ብልጭ አልል ብሎኝ አለ። አንተን መግደሌንም እንደ እማስታውስ እጠራጠር አለሁ።

[በጊዜው ዙሪያ፣ ነቢውላ እና ደቦዋ ገሞራ ጀርባ ማሳደዱን እንደተያያዙት ነበሩ]

--------

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ክዊል፣ መፈናፈኛየለሽ ሆኜ አለሁ። ወደ ሚላኖው መድረስ እማልችል ነኝ። መሹለክ ግድይለኝ አለ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ቆይ! ቆይ! እነእዚህ ነገሮች ወደ እዚያ ለመዉጫነት የታለሙ አልነበሩም።

[ገሞራ ጎሬዋን ከከባቢአየሩ አናት ወሰደች ያኔም ኔቢውላ መከታተሏን ቀጠለች]

ነቢውላ (ኬረን ጂላን)

ማፈሪያ ነሽ፣ እህት። አብረን ከተወለድንአቸው ሁሉ፣ አንቺን እምጠላው ትንሹን ነበር።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ነቢውላ፣ እባክሽ... ሮናን ይህን ድንጋይ ያገኘው ከሆነ፣ እኛን ሁላችንንም ይገድለን አለ።

ነቢውላ (ኬረን ጂላን)

ሁላችንንም አይሆንም። አንቺ አስቀድሞ የሞትሽ ነው እምቶኚው።

[ነቢውላ እስኪፈረካከስ የገሞራ ጎሬን ተኮሰች በእዚያም በህዋው ከአለአየር ለመንሳፈፍ ተወቻት። ሩሩም ወደ እርሷ እንዲመጣ ተቆጣጥራ አዘዘችው]

[ሮናን ደብድቦት ሩህ የለቀቀ ድራክስን እየጎተተ በምድሩ ሲወስድ እንመለከት ሆነ እና በአንድ ቢጫ ፈሳሽ ታንከር ዉስጥ ወረወረው]

ነቢውላ (ኬረን ጂላን)

ሮናን፣ ተፈጽሞ አለ። 

[ነቢውላ ሮናንን ለመልቀም መጣች]

[በጊዜው ዙሪያ ጴጥሮስ እና ሮኬት ገሞራ አካሏን በከባቢአየሩ ሲንሳፈፍ ተመለከቱ] 

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ክዊል፣ ና እንጂ። ለተጨማሪ ሁለት ደቂቃዎች የሰዉነት ዘረዘዴ (ሞድ) ህልዉ አድርጎ ሊጠብቃት ይችል አለ። ዳሩ፣ እኛ ምንም ልናደርግ እምንችለው ነገር የለም። እኒህ ጎሬዎች እዚህ ዉጭ ለመሆን የታቀዱ አልነበሩም። ሰከንዶች ዉስጥ፣ አንድአይነት መርከብ ላይ ነው እምንሆነው።

[ሮኬት ጎሬውን አዞረ እና መመለስ ጀመረ]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ኤጭ! ትሽ!

[ጴጥሮስ ከ ጎሬው ለመዉጣት እየተዘጋጀ]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ክዊል?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

[ጴጥሮስ መልእክት ለዮንዱ ሰደደ]

ዮንዱ! ዮንዱ።

ይህ ክዊል ነው! የእኔ መተባበሪያአዊ ፪-፪-፯-ኬ-፪-፫-፬ ናቸው።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ክዊል! ክዊል፣ ምን ማድረጉ ላይ ነህ,?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ልክ ምንሙሥፍራ ዉጭ ነኝ። በእዚያ ካለህ፣ ና እና አግኘኝ። እንዳለ ያንተው ነኝ።

[ጴጥሮስ ጭምብሉን አጠለቀ፣ ወጣ እና ወደ ገሞራ አካባቢ አቀና]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ክዊል፣ ተላላ አትሁን። ወደግልህ ጎሬ ተመለስ! ሁለት ሰዎች ማብቃቃት አትችልም እዚያ ዉስጥ።

ትሞት አለህ! በሰከንዶች ሟች ነህ! ክዊል። 

[ጴጥሮስ የገሞራን አካል ያዘ እና ጭምብሉን ከፊቱ ማላቀቅ ጀመረ]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

[ጴጥሮስ ጭምብሉን በገሞራ ፊት አጠለቀ እና መተንፈሱን ጀመረች፣ ከእዛ የዮንዱ መርከብ እየደረሰ ቀረበ እና ጴጥሮስ እና ገሞራን ከመሞትአቸው ቀደም ብሎ አገኘአቸው]

[ወደ ዮንዱ መርከብ ሲዘልቁ ገሞራ እራሷን አወቀች ያኔም ድረስ ጴጥሮስ እንደያዛት ነበረ]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ክዊል? ምን ተከስቶ ነበር?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እዚያ በዉጭው አንቺን ተመለከትኩሽ። ምን እንደነሸጠኝ አላውቅም። ብቻ ትሞቺ ዘንድ  ማድረጉን አልቻልኩትም። እግሌ ዉስጥ የሆነ ነገር አገኘሁ። የሆነ... እሚከብድ ጀግንነት። ማለቴ፣ ለመኩራራት አይደለም፣ ግን እንደ ገሃዱ ከሆነ...

[ገሞራ በብስጭት እህታ አሰማች]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ሩሩ ወደየት አለ?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ያ... ደህና፣ ሩሩን አጊንተውት አለ።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ምን?

[ልክ ያኔ አንድ በር ተከፈተ እና የዮንዱ ሰዎች ሰረጉ]

የዮንዱ ታዛዥ

እንኳን ደህና ወደቤት መጣህ፣ ጴጥሮስ።

----

[ግሩት ድራክስን ከቢጫው ፈሳሽ በማውጣት አድኖ እንዲተነፈስ አገዘ፣ ሮኬት ከእዛ ጎሬውን ፊትለፊቱ አሳረፈ እና ከዉስጡ እራሱን አወጣ]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ጥምብዝ ደደቦች። ሁሉም ቂሎች ናቸው! ክዊል እራሱን አስማረከ።

[ለድራክስ]

ምኑም ከእዚህ አንዱ አይከሰትም ነበር አንተ በአንድ እራስህ ብቻ ሙሉ ጉደኛ ሠራዊት ልታወጣ ባትሞክር ኖሮ!

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

ልክ ነህ። ቂል ነበርኩኝ። ሁሉም ቁጣ፣ ሁሉም ንዴት፣ ማጣቴን ለመክደን ብቻ የነበረ ነበር።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ዉይ ቡሁሁሁ። “የኔ ሚስት እና ልጅ ሞተው አሉ።”

[ግሩት እህታ በድንጋጤ አወጣ ይህም በሮኬት ለሰው ስሜት ዋጋ አለመስጠቱ ላይ ለማሳበቅ ታቀደ]

ዴንታዬ አይደለም ኢጨዋ ከሆነ! ሁሉም የሞቱ ሰውዎች ያሉት ነው። ያ የቀሩትን ሁሉ በሂደትህ እንዲሞቱ ምንም ማመካኛ አይደለም!

[ገስፋቆርጦ ለግሩት]

ና፣ ግሩት!

ሮናን ድንጋዩ አለው።

ያለን ብቸኛው ዕድል ወደ ሌላኛው ቤተክዋክብቱ ጎን በእሚቻለው ፍጥነት መድረስ እና ምንአልባት፣ እንደው ምንአልባት፣ ሙሉ ሂወት እንኖር ዘንድ እዚያ እንደርስ ይሆን አለ ፣ ያ ቅጥር-ማጅራትመቺ እዚያ ከመድረሱ ቀድመን።

ግሩት (ቪን ዲዝል)

[ግሩት በመቃወም እራሱን አነሳ]

እኔ ግሩት ነኝ።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

እንቆጥብአቸው? እንዴት?

ግሩት (ቪን ዲዝል)

እኔ ግሩት ነኝ።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

አዉቅአለሁ ብቸኛ የነበሩን ጓደኛዎች እነርሱው ናቸው፣ ዳሩ የራቬጀሮች ሠራዊት በዙሪያአቸው አለ። እና እኛ ሁለትአችን ብቻ ነው ያለንው!

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

ሦስት!

[ድራክስ ተነሳ እና ከግሩት ጎን ቆመ]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

[ሮኬት በመናደድ ዞር ሲል አጠገቡ ያገኘውን ያበጠ መሬት መደብደብ ጀመረ]

ሣር...

እንድጠልዝ…

እያደረግከኝ….

ነው!

--------

ጨለማው አስተሩ ዉስጥ


[ሮናን መርከብ ጨለማ አስተሩ ዉስጥ ሮናን ታኖስን በምስልአዊ ደውሉ በኩል ማናገር ላይ ሆነ]


ሮናን (ሊ ፔስ)

ሩሩ እኔ ይዞታ ዉስጥ ነው፣ ቃልእንደተገባው።

[ኮራት ሩሩን በእጅ አቀረበ]

ታኖስ (አሌክሲስ ዴኒስኦፍ)

[በገጽማያው የተገለጠ ታኖስ በእርጋታ ሆኖ]

ወደ እኔ አምጣልኝ።

ሮናን (ሊ ፔስ)

አዋ፣ ያ ስምምነትአችን ነበረ።

[ሮናን ሩሩን ከኮራት ወሰደ]

እኔ ሩሩን ላምጣልህ፣ አንተ ዛንዳርን ለእኔ ታጠፋልኝ አለህ።

ቢሆንምእንኳ፣ አሁን ኁልቆመሣፍርት ድንጋይ እንዳስተናገደ አዉቄ አለሁ እና፣ ያልገባኝ ምን ጥቅም ለአንተ እንደእምሰጥህ ነው።

[ሮናን ሩሩን ከፈተ እና በዉስጡ ኁልቆመሣፍርቱ ድንጋይ ላይ ተመለከተ]

ታኖስ (አሌክሲስ ዴኒስኦፍ)

ልጅ! እኔ ብሆን የወቅቱን አካሄድክን ዳግ-አጤነው ነበር።

ኮራት (ጂሞን ሆውንሱ)

[ኮራት ደነገጠ]

ጌቶች! ኧረ አይችሉም!

ህዋው ዉስጥ ከሁሉ ጉልበትአሙ ፍጥረት ታኖስ ነው።

ሮናን (ሊ ፔስ)

ከእንግዲህ ወዲህስ አይሆንም!

[ድንገት ሮናን ኁልቆመሣፍርት ድንጋዩን አዉጥቶ ጉልበቱን ከሰዉነቱ እያሰረገ ቆይቶ ለዉጊያመዶሻው አጣበቀ እና አጋራው። ጉልበቱን በሰውነቱ መጥጦ ኃይሉን ጨመረ]

እኔን “ልጅ” ብለህ ትጠራኝ ዘንድ አለህን!

ዛንዳር ላይ የ፻፻ ዓመቶች ክሪ ፍትሕ እፈለቅቅበት ዘንድ አለሁ፣ ታዲያ የምድሩ ሆድዕቃ ድረስ አነድደው ዘንድ ነው።

ከእዚያ ወዲያ ታኖስ፣ እመጣልህ አለሁ ለአንተ።

[ጥሪውን ዘጋ]

ነቢውላ (ኬረን ጂላን)

[ነቢዉላ ግራተጋብታ]

ከዛንዳር በኋላ፣ የኔን አባት ልትገድለው ነው?

ሮናን (ሊ ፔስ)

ትደፍሪ ዘንድ ልትቃወሚኝ ሆንሽን?

ነቢውላ (ኬረን ጂላን)

ወደ ምን እንደቀየረኝ ትመለከት ይሁን። እሱን ከገደልክው፣ አንድሺህ ፈለኬዎች መደምሠስ እማግዝህ ነኝ።

--------

ዮንዱ መርከብ ዉስጥ


[ዮንዱ መርከብ ዉስጥ፣ ዮንዱ ጴጥሮስን እየጠፈጠፈ ነው፣ እርሱም በዮንዶ ሰዎች የተጠፈነገ ነበር] 

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

አንተ እኔን ትከዳ አለህ?

ብሬን ትሠርቀኝ አለህ?

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

አቁመው! ብቻውን ተወው!

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

እንደ ልጅ ሣነሳህ እነእዚህ ልጆች ሊበሉህ ፈልገው ነበር። ቀደሞብለው ምንም ታራን ቀምሠው አያቁም ነበር። ህይወትህን አዳንኩ!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ኧረ ስለእዛ አፍክን ትዘጋ አለህን? አቤቱ እግዚእአብሔር! ሃያ ዓመቶች፣ ያን ፊቴ ላይ ስትለድፍብኝ ነበር፣ እኔን አለመሰልቀጡ የሆነ ታላቅ የሆነ ነገር ያክል። መደበኛ ህዝቦች ሌላውን መብላት ቀርቶ አያስቡትም እንኳ!

እጅግ ያነሰ ነው ጭራሽ ስላልበሉህ ሊመሰገኑበት መፈለጉ እማ!

አገትከኝ አንተ፣ ሰውየው!

ከቤቴ እና ከቤተሰቦቼ ሠረቅከኝ!

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

አንተ ስለ ታራህ ዴንታ የለህም! 

[ዮንዱ ጴጥሮስን ደረቱ ላይ መታው]

የደነገጥክው እዚህ ዉስጥ ደካማ ስለሆንክ ነው!

እዚህ! እዚህ ዉስጥ!

[ዮንዱ ሊመታው ደግሞ ጴጥሮስን አጥብቆ ያዘ]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ዮንዱ። አድምጠኝ!

ሮናን አንድ ኁልቆመሣፍርት ድንጋይ እሚሰኝ አጊንቶ አለ።

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

ምን እንዳገኘ አዉቅ አለሁኝ፣ ሴት።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ከሆነ፣ መልሰን ማግኘት እንዳለብን ታውቅ አለህ!

ዛንዳርን ለማጥፋት ሊጠቀምበት ነው። 

ልናስጠነቅቅአቸው ይገባን ዘንድ ነው። ቢሊየን ህዝቦች ይበሰብሡ አሉ።

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

[ለጴጥሮስ ገሞራን ልኮት ደየሰጠው]

ያን ነበር ጭንቅላትህን ስትሞላበት የነበረው፣ ልጅ?

ስሜት?

[ዮንዱ ጴጥሮስን አጮለው እና የዮንዱ ሰዎች ሳቁ]

እንደ ሥጋትል ጭንቅላትህን ስትበላው? በቃ ይህ ነው።

[ፈላፃውን እንዲበርር እያዘዘው ወደ ጴጥሮስ መሰልቀጫ ላይ አነጣጠረበት]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

አይሆንም!

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

ይቅርታ። ልጅ። እኒያ እሚቃረኑት ምን እንደእሚገጥምአቸው ለሰዎቹ አንድ ሻምበል ግን ለማስተማር ይገባው ዘንድ ነው።

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

ሻምበል እሚያስተምረው አንድ ጉዳይ አጊንቶ አለ!

[ሌላዎቹ በመስማማት ጉምጉምታ ሰጡ]

ሁሉም የዮንዱ ታዛዦች

አዎ። አዎ!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አሁን እኔን ከገደልህ፣ ከአየህአቸው ሁሉ ለትልቁ ልዩነጥብህን ደህና ሁን እያልክው ነው።

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

[ዮንዱ ፈገግ አለ እና ፊቱን ሊመለከት ወደ ጴጥሮስ ዞረ]

ድንጋዩ?

ተስፋ አደርግአለሁ የሆነ ከእዛ እሚሻል እንዳገኘህ።

ምክንያቱም፣ ማንም ከሮናን እሚሰርቅ አይደለም።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አንድ መልሶ-ተፃራሪ አጊንተን አለ።

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

ያ ትክክል ነውን?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ስለሮናን ሊታወቁ እሚችሉ ሁሉ ነገሮችን ፣ እሷ ታውቅ አለች። መርከቦቹን! ሠራዊቱን!

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

እሱ ለጥቃትእሚወድቅበት አለው!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እሺ፣ ምን ትልአለህ፣ ዮንዱ?

እኔ እና አንተ፣ ጎን-ለ-ጎን ለመሯሯጥ፣ እንደ ጥንቶቹ ቀኖችአችን!

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

[ዮንዱ ለቅጽበቶች አሰብ እያደረገ አቅማማ፣ ከእዛ አፏጨ እና ፈላፃው መልሶ ከጴጥሮስ መሰልቀጫ አካባቢ ወደ አፎቱ ተመለሰ]

[ዮንዱ እና ሰዎቹ ሁሉ መሳቅ ጀመሩ]

ሃሃሃ... ልቀቁት ይሂድ!

[ጴጥሮስን ቀላቀሉት]

ሁሌም አንድ (ቆለጥ)ከረጢት አለህ፣ ልጅ! ለእዚያ ነበር እንደ ታዳጊ ያቆየሁህ!

ክራግሊን (ሲያን ጉን)

 [ልክ ያኔ መርከቡ በአንድአች ነገር ሲቀወር ተነቀነቀ]

ሻምበል፣ ተኩሱ ኢጎጂ ነበር።


[ሚላኖዋ ወደ ዮንዱ መርከብ ስትቀርብ ተመለከትን]


ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

አተኩሩ፣ ደደብዎች!

እዚህ በራሪ አናት ላይ ያለው ቀዉሱ አንድ ሀድሮን ማስፈንጠሪያ የተሸከመ ነው።

[ድራክስን በአንድ ህዋልብስ (ስፔስ ሱት) ሚላኖው አናት ላይ ተሰቅሎ መሳሪያ ይዞ ተመለከትን]

በንድፍነቱ ፣ የግሌ መሳሪያ ነው።

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

ኧረ የምን ጉድ?

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ባልንጀሮችአችንን እማታስረክቡ ከሆነ አሁን፣ መርከብአቹህን ወደ አንድ አዲስ ይበጣጥሰው አለ። በጣም ትልቅ አዲስ!

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

ለኔ አይነፋኝም!

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

የአምስት ቆጠራ እየሰጠሁአችሁ ነው። ፭፣ ፬፣ ፫...

[ጴጥሮስ እና ገሞራ ክራግሊን ሚላኖው እንዲተኮስበት ዕዝ መከወኑን እዲአቆም አሳወቁት]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አይሆንም።

ገሞራ (ዞይ ሶልዳና)

አይሆንም፣ ቆይ፣ ያዘው!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ሮኬት!

እኔ ነኝ፣ ስለእግዚእአብሔር ብለህ!

ዘይደንለት አለ! ደህና ነን!

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

እንዴ እሺ፣ ክዊል። ምን እየተካሄደ ነው?

--------

[ዮንዱ መርከብ ዉስጥ እነሮኬት ተቀላቅለውአቸው አንድ ሆኑ]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ያንን “ዘይደንለት አለ” ብለህ ትጠራው አለህ? ልክ አሁን ትርጉምወደማጣትነት የደበደቡንን ሰዎችን ልንዘርፍ ነው።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ስለትርጉምየለሽነት ማዉራት ትፈልግ አለህ? እኛን በማፈንዳት እኛን ማዳን ስለመሞከሩሳ?

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ልናፈነዳአችሁ የነበርንው እማያስክቡአችሁ ከነበረ ብቻ ነው!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እና በዚች ምድር ላይ እንዴት እነእርሱ ሊያስረክቡን ይችሉ አሉ፣ የሰጣችሁት አምስቴ ቆጠራ ብቻ ሆኖ?

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

የዕቅዱን ስምጥ መዉጫ-መግቢያ ለማብላላት ጊዜ አላገኘንም ነበር!

ይህን ነው እምናገኘው በደጉሳምራዊነት ስለተንቀሳቀስን።

ግሩት (ቪን ዲዝል)

እኔ ግሩት ነኝ።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ኢአመስጋኞች ናቸው።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

አሁን ጠቃሚው ነገር ፣ ዛንዳርን ለማዳኑ የራቬጀሮች ሠራዊትን አጊንተንአቸው አለ።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ታዲያ ድንጋዩን ለዮንዱ ልንሰጠው ነው እሱም ለሆነ ባሽ ሊሸጠው ነው?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ያን ክፍል ኋላ እምንዘይድለት ነው።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ሮናንን ማስቆም አለብን።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

እንዴት?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አንድ ዕቅድ አለኝ።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

አንድ ዕቅድ አለኝ?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አዎን።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ከሁሉ መጀመሪያ፣ እኔ አንድ ዕቅድ አለኝ ከእምለው እየኮረጅከኝ ነው።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አይደለም፣ አልቀዳኹህም። ህዝቦች ያን ሁልጊዜውንም ቢሆን እሚሉት ነገር ነው። ያን ያክል ሲናገሩት ከቶ የተለየ ነገር አየደደለም።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ሁለተኛ፣ አንድ ዕቅድ እንዳለህ ሁሉ እራሱ አላምንህም።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

የአንድ ዕቅድ ክፍል አለኝ!

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

የአንድ ዕቅድ፣ ምንያክል እጅ አለህ? 

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

[ተቆጣችው]

ምንሙሥፍራ ዉስጥ ከመዘዝክው እርባናቢስነት በኋላ አንዲት ጥያቄ ልትጠይቅ እሚገባህ አቶናትም!

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

ልክ አሁን ክዊልን አዳንኩኝ እኮ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ቀደምብሎ፣ እናንተ የነበርኩበት መርከቡን በመደምሰሥ እኔን ልታድኑ ያደረጋችሁት እኔን ከመቆጠብ እንደማይቆጠር እንደሆነ አቋቁመን አለን። 

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

መች ነው ያቋቋምንው የነበረው?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ሦስት ሰከንዶች ብጤ ቀድሞ!

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

እያደመጥሁ አልነበርኩም።

እኔ ሌላ ነገር ሳብሰለስል ነበር።

ገሞራ (ዞይ ሶልዳና)

[በመናደድ]

እህ!

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ትክክል ናት እሷ።

አንተ ሃሳብ ማቅረቡ አይገባህም።

[ለጴጥሮስ ዳግ-ቀጥሎ]

ምን ያክል መቶኛ?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አላውቅም! አስራሁለት መቶኛ።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

አስራሁለት መቶኛ?

[ሮኬት ሳቁን አዉካክቶ ለቀቀ]

ካ...ካ....ካካካ.....

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ያ ሀሰተኛ ሣቅ ነው።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

የምር ነው!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ሙሉበሙሉ ሀሰተኛ!

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ያ፣ በመላ ዘመኔ ከነበሩት ሁሉ ከሁሉም ከምር፣ እቅጭ፣ ስሜትፈርአዊ (ሂስተሪካል) ሣቄ ነው።

ምክንያቱም ያ፣ ስለ ዕቅድ አልሆነ። 

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ጽንሠሃሳብ እንኳ መሆኑ አዳጋች ነው።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

የእነሱን ጎራ እየወሰድሽ ነው?

ግሩት (ቪን ዲዝል)

እኔ ግሩት ነኝ።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

እና ምን፣ ከ፲፩% የእሚሻል ነው?

ያ ከምንስ ነገር ጋር ምን እሚያገናኘው ነገር አለ እና ነው?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አመሰግን አለሁ፣ ግሩት። አመሰግን አለሁ።

ተመለከትአችሁ? ግሩት ከእናንተ መሀከል ፍንጭ ያለው ብቸኛው ነው።

[ጴጥሮስ ወደ ግሩት ተመለሰ እና ተመለከተው እርሱም ከግሉ ትከሻው የሰገገ ቅጠልን ቀመስ አድርጎ ማመንዠኽ ጀመረ፣ ጴጥሮስ አናቱን ሲወዘውዝ እህህታ ሮኬት አሰማ]

ሠዎች። ኑ እንጂ። ዮንዱ ሁለት ሰከንዶች ዉስጥ እዚህ እሚሆን ነው። ይሄን የእኛን ትልቅ ዕቅድ እሚጠብቅ ዘንድ ሆኗል። እርዳታአችሁን እፈልገው ዘንድ ነው። እኛ መሀልአችንን ዞሬ እመለከት አለሁ። ምን እንደእምመለከት ታዉቁ አላችሁ? ተሸናፊዎች!

ማለቴ፣ እንደ፣ ነገሮች የተነጠቁ ጎበዞች። እና ተነጥቀን አለ። ሰዉ ሆይ፣ የተነጠቀን አለን። ሁልአችንም። ቤቶችአችንን፣ ቤተሰብዎችአችንን፣ መደበኛ ኑሮአችንን። እና፣ ምንጊዜም፣ ከእሚሰጠው በላይ ሂወት ወሳጅ ነው። ነገርግን ዛሬ አይደለም። ዛሬ፣ አንድአች ነገር ቸሮን አለ። አንድ ዕድል ሰጥቶን አለ።

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

ምን ለማድረግ?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አንድ ዴንታ ለመስጠት!

ለአንዴ። ሸሽቶ ላለመሮጥ!

እኔ፣ እንደ አንዴ፣ ቆሜ ሳለሁ ሮናን ንጹሐን ቢሊየኖች ነብሶችን ሲጠርግ  አልታገስም።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ግን፣ ክዊል፣ ሮናንን ማስቆም፣ ያ ኢኋኝ ነው። እንድንሞት እየጠየቅከን ነው።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አዎን፣ እንደምገምተው ነኝ።

[ጴጥሮስ በመሸነፍ ጀርባውን ለደቦው መለሰ]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ክዊል። የሂወቴን አብዛኛ ክፍል በጠላቶች ተከብቤ ኖሬው አለሁ።

[ከተቀመጠችበት ተነስታ በእግሮቿ ላይ ተቆለለች]

በጓደኛዎቼ መሀከል ብሞት ኩራት እሚሰማኝ ነኝ።

[ድራክስ በእግሮቹ ተቆለለ]

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

አንተ የክብር ባለቤት የሆንክ ሰው ነህ፣ ክዊል። ጎንህ ጋር እፋለም አለሁ። እና በመጨረሻው፣ ሚስቴን እና ልጄን ደግሜ እመለከት ዘንድ አለሁ።

[ግሩት ቀጥሎ ቆመ]

ግሩት (ቪን ዲዝል)

እኔ ግሩት ነኝ።

[ከእዚያም እነእርሱ ሁሉም የቀረው ሮኬት ላይ ተመለከቱ፣ እርሱም በመጨረሻ፣ እህታ አሰማ እና ተሸነፈ]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

እህ... ምን አባቱ!

ያን ያክል እረዥም የእድሜ-ጣሪያ የሌለኝ ነኝ፣ በእዚያም አለ በእዚያ። 

[ሮኬት እንዲሁ ተነሣ እና በመቀመጫ ወንበሩ ላይ ቆመበት]

አሁን እተገትሬአለሁ። ሁላችሁ ደስተኛ ሆናችሁ? ሁላችንም ተገትረንአለ አሁን፣ የሀሬዎች ደቦ፣ በክብ ዙሪያ ቆመን።

[ሙዚቃ ይጫወት አለ ይህም ድንጋዩን ከሮናን ስለመዝረፍ ዕቅድን ሲያበጁ ሆነ]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

[በፊትአቸው እየተረማመዱ ማስረዳት መነጋገሩን ጀመሩ]

ድንጋዩ ማንኛውም የነካው ነፍስአማ ነገር ላይ ዳግ-መላሽ (ሪአክሽን) ከዋኝ ነው። የእሚነካው በገዘፈ ቁጥር፣ ጉልበቱ ያሻቅብ አለ!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ሮናን ማድረግ እሚጠበቅበት አንድ ነገር ቢኖር ድንጋዩን በፈለኬው ገጽ ላይ መንካት እና እሱ ይደመሥስለት አለ። ሁሉም ተክሎች፣ እንሰሳዎች፣ ኖቫ ጓዶች ይሞቱ አሉ።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ሁሉነገር ሟች ይሆን አለ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ስለእዚህ ሮናን ወደ ገጸምድሩ መድረስ የለበትም።

--------

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ዳርክ አስሩ ዉስጥ አንድ ቀዳዳ ለመቦርቦር ሮኬት አንድ ደቦ እሚመራ ይሆን አለ። የአካለ መርከቡ ቀኝ በኩል። ከእዚያም፣ የእኛ በራሪ እና የዮንዱው ይሠርግበት አለ።

የዮንዱ ታዛዥ

በመቶ እሚቆጠሩ ሳካራን ወታደሮች በዉስጥ በኩል አይኖሩምን?

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

እኔ ሳካራንዎችን እንደ ወረቀት ሰዎች ነው እምቆጥርአቸው።

[ክራግሊን ሳቀ እና ድራክስን በትከሻው ጓደኛአዊ ቸብታ ሰጠ፣ ዳሩ የጨዋታውን መለፋደድ ድራክስ ሳይገነዘብ፣ ክራግሊንን እሚመታው መሰል ብሎ ተመለከተው። ክራግሊን ደነገጠ]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

እኛ እንደተሳፈርንብአቸው ልክ እንደተገነዘቡ፣ ከእማይሠረሰር ደህንነት በሮች ጀርባ በዴስኩ ዉስጥ ሮናን ግሉን ይወሽብ አለ። የኃይል ምንጩን በመበታተን እኔ ያንን አጠፋው ዘንድ አደርግአለሁ ነው። 

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ወደ በረራው ዴስክ እኔ እደርስ አለሁ እና የሀድሮን ማስፈንጠሪያውን ተጠቅሜ ሮናንን እገድለው አለሁ።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

አንዴ ሮናን እንደሞተ፣ ድንጋዩን እንለቅም አለን። ለመጠቅለል እነእዚህን መሣሪያዎች ተጠቀሙ።

[የሚመሳሰሉ ሩር መሳሪያዎች ለሁሉም ታደሉ]

በእጅ ከነካችሁት እሚገድልአችሁ ይሆን አለ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እኛን ከአሰሩት ዉስጥ አንዱን የኖቫ ጓድ እኔ እምደርስበት ይሆን አለ። በተስፋ፣ እዚያ ለርዳት እንደምንገኝ ያምኑን አለ።

[ጴጥሮስ ዴይን ሊገናኝ ሲሞክር እንመለከት አለን]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ዕቅዱን ለማሟላት አንድ ተጨማሪ ነገር ያስፈልገ አለ።

[ወደ ዮንዱ አንዱ ታዛዥ ሰው ጠቆመ እርሱም የሰቤአዊ ዓይን ተክሎ ነበር]

 የእዛ ሰውዬ ዓይን።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አይ! አይ፣ አንፈልገውም። አይ፣ የእዛን ሰዉዬ ዓይን አንፈልግም።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

አይ፣ ከምሬ ነው፣ እኔ እፈልገው አለሁ! ያ ለእኔ አስፈላጊ ነው።

[ሮኬት ሳቀ]

--------

የሮናን መዉጊያ-በራሪ ተነጥቦ አለ፣ እና ደራሾች ከሆንንበት አስራአምስት-ደቂቃዎች ቅናሽ (ቲ-፲፭) ላይ ነን።

--------

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

[ለጴጥሮስ]

አስታውስ፣ ልጅ። ከእዚህ ሁሉ ማብቂያ በኋላ፣ ድንጋዩን እኔ ወሳጁ እሆን አለሁ።

ተሳፈጠኝ እና ሁላችሁንም እምንገድል ዘንድ ይሆን ነው!

[ከመዘጋጀት በኋላ፣ ጴጥሮስ እና የቀሩት ቡድን በመርከቡ መረማመድ ጀመሩ]

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

እንሂድ! 'ናግኛችው ልጆች!

[ትንንሽ በራሪጠለልዎች (ኤየርፕሌንስ) ከዮንዱ ዋና በራሪቅርጽ ወጡ። እነጴጥሮስ በእራስአቸው፣ በሚላኖው፣ መርከብ ሆነው ወጡ]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ይህ የከፋ አስደንጋጭ ዕቅድ ነው።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እንዴ፣ አንቺው ራስሸ ነበርሸ በጓደኛዎች መሀከል ሆኖ ለመሞት የፈለግሽው።

--------

[ኖቫ ጓዶች ዉስጥ፣ ዴይ ቀዳሚት ኖቫን ለማሳወቅ ቀረበ]

ኮርፕስማን ዴይ (ዮሐንሥ ሲ/ሬሊ)

ኖቫ ቀዳሚ። ከራቬጀሮቹ ከአንዱ የሆነ ስርጭት ተቀብዬ አለሁ። እሱ እሚለው ፣ የሆነ ኁልቆመሣፍርት ድንጋይ እሚባል ነገር ሮናን ይዞታ ላይ ነው። እና ወደ ዛንዳር እያቀና ነው።

ኖቫ ቀዳሚት (ግሌን ክሎስ)

ኧረ እግዚእአብሔር ሆይ!

ዴናሪያን ሳል (ጴጥሮስ ሠራፊኖዊክስ)

ማታለያ ነው።

ወንጀለኛ ነው እሱ።

ኖቫ ቀዳሚት (ግሌን ክሎስ)

ለምን ልናምነው እንደሚሻለን የተናገረው አለን?

ኮርፕስማን ዴይ (ዮሐንሥ ሲ/ሬሊ)

የእሱ ደቦ ከእስርቤት ልክ አምልጦ ነው ያለው እና ወደ ዛንዳር ለእርዳታ መጥቶ እምቅአደጋ (ሪስክ) ውስጥ እሚገባበት ምንም አመክዮ የለም ብሏል። “ቂ-ቀዳዳ” ነኝ ብሎ አለ። ነገርግን፣ እና እጠቅሰው አለሁ እዚህ ጋ፣ “፻% ቁላ” ግን አይደለም።

ኖቫ ቀዳሚት (ግሌን ክሎስ)

አንተ ታምነው አለህ?

ኮርፕስማን ዴይ (ዮሐንሥ ሲ/ሬሊ)

እኔ ማንም  ፻% ቁላ እንደሆነ አላምንም፣ እናቴ።

ኖቫ ቀዳሚት (ግሌን ክሎስ)

ማለቴ፣ እዚህ ሊረዳ እንደመጣ አንተ ታምነው አለህ?

[ከመመለስ ቀድሞ ዴይ ለቅጽበት አመነታ እና ተናገረ]

ኮርፕስማን ዴይ (ዮሐንሥ ሲ/ሬሊ)

አዎን።

--------

[ሮናን መርከብ ዉስጥ]

ነቢውላ (ኬረን ጂላን)

አንድ በራሪአካል ተዳረሰ። ራቬጀሮች ሆነው ተገለጡ።

[ጨለማ አስተሩ ጋር ደርሰው የነዮንዱ መርከቦች ተሰተሩ]

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

ተኩሱ!

ሸፍኑት!

[መርከብዎቹ ጨለማ አስተሩ ላይ ተኮሱ። እና የተኮሱት ፍንዳታዎቹ የእሳት ጭጋግ ወልደው ከመርከቡ በመጣበቅ ረበቡበት]

ስመጡ!

[መርከብዎቹ፣ ሚላኖውን ጨምሮ በጭጋግ ያጨለሙትን መርከብ በማታመል ከቂጡ በኩል ዝቅ ብለው ተከልለው ወደ ጨለማ አስተሩ ቂጥ አለፉ]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ሮኬት፣ ፍጠን!

[መቦርቦሩን ለመከወን ስለተመቻቸለት ይጠብቁት ጀመረ]


[ነቢውላ ጭጋጉን ተመልንታ ቆየች እና ጨዋታው ሲገባት ጨለማ አስተሩ ላይ ላለው የሮናን ደቦ ዕዝ ሰጠች]

ነቢውላ (ኬረን ጂላን)

ሁላችሁም አብራሪዎች፣ ስመጡ!

ከስርአችን ናቸው!

------

[ኖቫ ጓዶች ዋና ጽሕፈት ቤት ዉስጥ]

ኖቫ ቀዳሚት (ግሌን ክሎስ)

ከተማውን አስለቅቁት!

ቀዳሚ እምናደርገው ህዝብአችንን ከጦር ዉድማው ማራቁ ነው።

[ለደቦዋ የራቬጀሮች መርከብዎች እና ሚላኖዋ ጨለማው ላይ ሲተኩሱ]

ነቢውላ (ኬረን ጂላን)

ወደፊት ታገሉ፣ አሁን!

--------

የዮንዱ ታዛዥ

ና እንጂ!

[ጨለማማ አስተሩ ዉስጥ ሽንቁር ማዉጣት ከቻሉ በኋላ]

--------

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ክዊል! ዮንዱ! አሁን!

[የዮንዱ መርከብ በመሳሪያ ተተኮሰች እና መከስነስ ጀመረች]

[እነጴጥሮስ ሮናን መርከብ ዉስጥ ለመግባት መሞነሩን ይቀጥሉ አሉ]

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

[ለእራሱ በንዴት]

ምንአባቱ!

[ለጴጥሮስ በመልእንቱ መስመር]

እየወደቅኩ ነው፣ ክዊል!

ከእኔ ጋር ከንግዲህ ቀልድ የለም፣ ልጅ!

በእዚህ ማብቂያ ላይ እምመለከትህ ይሆን አለ!

[ጴጥሮስ፣ ገሞራ፣ ድራክስ እና ግሩት ሮናን መርከብ ዉስጥ ለመግባት እስካሁን እየሞከሩ ነው]

[የሮናን መርከብ እሚተኩስብአቸው በራሪዎች ላይ ልኮት እያደረገች]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

በጣም ብዙዎችአቸው ናቸው ያሉት፣ ሮኬት! እዚያ እላይ ፈጽሞ አንደርስም!

[ልክ ያኔ በድንገት የኖቫ ሠራዊት እየመጣ ተቀላቀለአቸው እና ከሮናን ሠራዊት መቃረኑን ያግዙአቸው አለ]

ዴናሪያን ሳል (ጴጥሮስ ሠራፊኖዊክስ)

ጴጥሮስ ክዊል። ይህ የኖቫ ጓዶቹ ደናሪያን ሳል ነው።

በእንተማህደር (ፎር ዘ ሪከርድ) ግን፣ እኔ አንተን ማመኑን ተፃርሬ ነበር ምክሬን ያቀረብኩት።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

የ “ቁላ” መልእክቴን አገኙት!

ዴናሪያን ሳል (ጴጥሮስ ሠራፊኖዊክስ)

እኔ ስህተት እንደነበርኩ አረጋግጥ።

[ከኖቫ ጓዶች ከተገኘው ድጋፍ ጋር ጴጥሮስ መርከቡን በሽንቁሩ አሳልፎ ጨለማ አስተሩ ዉስጥ ተነከረ]

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

እሰይ!

[በመጨረሻ ሮናን መርከብ ዉስጥ መስረግ አሳክተው ሲንሸራተቱ]

እሰይ! ሃሃ 

[ሐሴት]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

[ለጴጥሮስ]

እኛ እራሱ ኬቪን ቤከን ሆንን።

--------

ነቢውላ (ኬረን ጂላን)

[ለሮናን]

የመርከቡ ቀኝ ክንፍ ከርን (ቀላል መሣሪያ ታጣቂ) ተጥሶ አለ! ተሳፋሪ ገብቶብን አለ!

ሮናን (ሊ ፔስ)

መቃረብአችንን ቀጥሉ።

ነቢውላ (ኬረን ጂላን)

ግን የኖቫ ጓዶች ማጥቃት ጀምረው አለ።

ሮናን (ሊ ፔስ)

ልክ ገጹ ላይ ከደረስን ፣ እንዲያ ያለው ነገር ምኑም እሚያሳስብ አይደለም።

[ለበረኛዎቹ]

ነቢውላ (ኬረን ጂላን)

የደህንነት በሩን አሽጉ! አሁን!

[ለጠባቂው የሮናን ፉካ (ቻምበር) ክፍሉን ለቅቃ ስትወጣ]

ከጎዳናዬ ዉጣ!

[ሮኬት ከጨለማ አስተሩ ተመለከተ ያም በኖቫ ጓዶች እሚደበደብ የነበረውን ነው]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

አቤት ሰዉዬው!

ኖቫ ቀዳሚት (ግሌን ክሎስ)

ሁላቹም ኖቫ አብራሪዎች፣ ተቆላለፉ እና መከታ ማገጃ ቅረጹ።

ጥቁር አስተሩ ምድሩ ላይ መድረስ የለበትም!

[የኖቫ ጓዶች ታላቅ ድር መቅረጽ ጀመሩ]

ኖቫ አብራሪ ቁጥር አንድ

ተቆላልፌ አለሁ!

ኖቫ አብራሪ ቁጥር ሁለት

ተቆላልፌ አለሁ።

ተቆልፈን አለን።

[ኖቫ መርከብዎቹ ጨለማ አስተሩን በሸረቡት ድር እንዳይወድቅ አገቱት ፤ መርከቡ ዉስጥ ጴጥሮስ እና  ተጨማሪ ደቦው መርከብአቸውን ለቀቁ እና ወደ ጨለማ አስተሩ ዉስጥ በእግሮች አመሩ]

--------

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

[ጨለማ ነበር]

ምንም አይታየኝም።

[ግሩት አብረቅራቂ እኑስዎች (ፖርቲክልስ) ከሰዉነቱ ለቅቆ መንገዱን እንዲያስመለክቱ ተገለገለአቸው]

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

[ሁሉም ተገርመው ተመለከቱ]

መቼ ነው ያንን ማድረግ የተማርክው?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

በጣም እርግጠኛ ነኝ መልሱ “እኔ ግሩት ነኝ” ነው።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

የበረራ ወለሉ ፫፻ ሜትሮች በእዚህ መንገድ እርቆ አለ። 

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

እንድታውቁ እፈልግ አለሁ ድህረ-ጅልስህተቴ እኔን ለመቀበልአችሁ በጣም አመስጋኝ ነኝ። አሁንም ድጋሚ ጓደኞች ማግኘቱ ሀሴት እሚሰጠኝ ነው። አንተ፣ ክዊል፣ የኔ ጓደኛ ነህ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አመሰግን አለሁ።

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

ይህ ጀዝባ ዛፍ፣ እሱ የእኔ ጓደኛ ነው። እና ይቺ አረንጓዴ ሸርሙጣ፣ እሷ፣ እንዲሁ...

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ታቆም ዘንድ ይሁን!

[ነቢውላ ዝግመትአቸውን ከፊትአቸው በመብቀል አስጣለች]

ነቢውላ (ኬረን ጂላን)

[እህቷን]

ገሞራ፣ ምን እንዳደረግሽ እስኪ ተመልከች።

ሁልጊዜም ቢሆን ደካማ ሆነሽ ነበር።

አንች ደደብ፣ ከሃዲ...

[ድንገት ድራክስ ነቢውላ ላይ ተኩስ ሰጠ እና ሳትጨርስ አብርሮ ላካት]

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

ማንም የእኔን ጓደኛዎች እንደእዚያ አይናገርም።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ወደ በረራው ወለል አቅኑ። የደህንነት በሮቹን ኃይል እኔ እዘጋው አለሁ።

[ዛንዳር በአለ ዐብይምድር (ሜይንላንድ) ዮንዱ ከተከሰከሰ በኋላ ትንሾቹን ቆንጅዬ ነገሮቹን ያነሳ አለ። በሮናን ሰዎች ተከበበ]

ጭምብልየለሽ ሳካራን የሮናን ታዛዥ

ዮንዱ ዑዶንታ።

ሠዎችህን ወደ ኖቫ ጓዶች ተፃራሪነት እንዲመለሱ ዕዝ ስጥ!

[ዮንዱ ማፏጨት ጀመረ ያም ፈላፃ መሳሪያውን አነቃ እና መብረር ጀመረ]

ራቬጀሮች-እማይረባነቱ ይብቃችሁ! ጊዜ ለሞት...

[ዮንዱ ዳግ-ማፏጨት ጀመረ እና ፈላፃው መሳሪያውን አሽከር አድርጎ የሻለቃ ቡድንዎች በሳስቶ አወደመ]

----

[በጨለማው አስተር ዉስጥ ገሞራ ወደ ወደቀች ነቢውላ አካባቢ ደረሰች ፣ እሷም የወላለቁ አጥንቶችዎችዋን እየገጣጠመች ነበረ]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ነቢውላ፣ እባክሽ!

[ገሞራ እና ነቢውላ ፍልሚያ ይቆሰቁሱ ዘንድ ሆነ ይህም የደህንነት በሮቹን ኃይል ገሞራ ልዘጋ ስትሞክር ሆነ]

ሮናን (ሊ ፔስ)

ይህስ ይበቃ አለ!

ኔክሮክራፍት አብራሪ፣ በንዳድ-መግደል ፈርምግባር (ኢንሼቲቭ) አስጀምር።

--------

ኖቫ አብራሪ

ከተማውን በመስመጥ-ቦንብ አጠቃቅ እየመቱት ነው!

ዴናሪያን ሳል?

አሠላለፍ እናፍርስን?

ዴናሪያን ሳል (ጴጥሮስ ሠራፊኖዊክስ)

አይ!

አሰላለፍአችሁን አቆዩት!

[የሮናን መርከብ ዛንዳርን ማጥቃት ተያያዘ]

--------

እነእሮኬት ከሮናን አስተር በመብረር እየወጡ ወደምድሩ ለመስመጥ እሚጓዙ መርከብዎችን ዝቅ ብሎ በመንሳፈፍ እየተኮሱ በአየሩ ማጋየት ተያያዙ]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

[መርከቡን ተጣብተው እሚሸክፉ እና በአየሩ ለማቆየት ለእሚጥሩት የኖቫ ቡድን መሪ ሳል]

ሮናንን እዚያ ከላይ ጠብቁ እና አቆዩአቸው፣ ሳል።

[እየኩአቸው ለሚመጡት ልኮት እየሰጠ]

እዚህ ከታች ያሉትን ህዝቦች እኛ እንንከባከብአቸው አለን።

ዴናሪያን ሳል (ጴጥሮስ ሠራፊኖዊክስ)

ከ ሀምስተር (አንድ የቤት እንስሳ አይነት) ዕዝ እየወሰድኩ እንደሆነ ማመን ያቅተኝ አለ።

[ጨለማ አስተሩ ዉስጥ የቀረው ቡድን በኮራት እና ቀሪው የሮናን ደቦ ተገጠሙ]

--------

ኮራት (ጂሞን ሆውንሱ)

[ለጴጥሮስ]

ኮከብ-ጌታ!

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

በፍፃሜ ላይ!

[መፋለሙን ተያያዙት]

ኮራት (ጂሞን ሆውንሱ)

አንተ ሌባ!

[ሁሉም ሲፋለሙ፣ ኮራት ድራክስን ወደ ጎን ወረወረ]

--------

ኮራት (ጂሞን ሆውንሱ)

ፈጽሞ ወደ ሮናን አትደርሳትም።

--------

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

[ለዮንዱ ደቦ ዕዝ እያሻገረ]

ሁላችሁም ምድሩን ከመምታትአቸው እየቀደምአችሁ ተኩሱአቸው።

[ሮኬት እና የዮንዱ ደቦ በሮናን ታዛዦች ላይ መተኮስ ተያያዙ። በጨለማ አስተሩ ደግሞ ገሞራ እና ነቢውላ በፍልሚያ መለየቱን ተያይዘውት እንደነበሩ አሉ]

ራቬጀር / የዮንዱ ታዛዥ

ኑ እንጂ!

[በጊዜው ዙሪያ ጴጥሮስ እና የቀሩት ደቦዎች ከኮራት እና ደቦ-ሮናን ጋር መፋለሙን፣ እና ድራክስ ኮራትን ለመያዝ ቻለ እና አናቱን ሊፈለቅቅብት ጀመረ]

--------

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

ጣት በአንገት ላይ ማለት ሞት ነው።

[ኮራትን ቀተለ እና ጴጥሮስ ወደ ድራክስ ተራመደ]

ፈሊጥ። 

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አዎ፣ ነገር።

[በድንገት የሮናን ተጨማሪ ደቦ ተከትሎአቸው ደረሰ]

ኧረ አይሆንም።

[ግሩት እጁን አርዝሞ የሳካራኖቹን ሆድዎች በመደዳው እንደ ብዙ መኮረኒ አንዴ እንደ እሚወጉት በአንድነት በስቶ ወጋአቸው እና ጓደኛዎቹን አዳናቸው። ከእዛም፣ የቀሩትን ሳካራኖች ለመጨረሥ እያውለበለበ በመመታታት ተጠቀመብአቸው። ባዶ ያደረገውን ስጋት ተደስቶበት ወደ ጴጥሮስ እና ድራክስ ዞረ እና ፈገግታ ሰጣቸው]

[ጨለማ አስተሩ ዉስጥ ሮናን ንግግር አወጣ ያም በኖቫ ዋናመስሪያቤት እሚደመጥ ሆነ]

--------

ሮናን (ሊ ፔስ)

ዛንዳር! ተከስሰሽ ቆመሽ አለ። ያንቺ መደዴው የሰላም ስምምነት አሁን እሚቆጥብሽ አይሆንም። የምትነድጂበት  ማያያዣው ነው።

[ሮናን ኁልቆመሣፍርት ድንጋዩን አነቃ ያም በጨለማ አስተሩ አካባቢ እሳት አቀጣጠለ ያም የኖቫ ጓዶች መርከብዎችን እሚደመስስ ሆነ የሳል መርከብን ጭምር]

--------

ዴናሪያን ሳል (ጴጥሮስ ሠራፊኖዊክስ)

ሮኬት!

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ያዘው ቆይ፣ ሳል፣ ብቻ፣...

[ሳል ተጨመቀ እና በሮናን መርከብ ስለተሸበለቀ ሞተ። ሮኬት ሌላዎቹንም ኖቫ መርከብዎች ሲደመስስ እሳቱን ተመለከተ]

ክዊል፣ መፋጠን አለብህ። ከተማው ከአደጋ ተለቅቆ አለ፣ ዳሩ እዚህ አካባቢ እኛ ቂጥዎችአችንን እየተደበደብን ነው።

[ጨለማ አስተሩ ዉስጥ፣ ጴጥሮስ ደቦ-ሮናንን መፋለም ቀጠለ። ያም ወደፊት ማቅናቱን እየቀጠለ ባስቆሙት ቁጥር እሚያደርገው ፍልሚያ ሆነ]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

በሩን ገሞራ አልከፈተችም!

--------

[ገሞራ እስከአሁን ነቢውላ ትፋለምአለች። በመጨረሻ ገሞራ ነቢውላን በጎኑ ከመርከቡ ዉጭ ለመገፍተር በቃች፣ ነቢውላ እጇ አንድ ነገር ላይ ይዞላት ጠርዙ ላይ ተንጠለጠለች። ገሞራ ከመርከቡ እንዳትወድቅ ልትረዳት ቀረበች]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ነቢውላ!

እህቴ!

ሮናንን መፋለሙን አግዥን። እብድ እንደሆነ ታዉቂ አለሽ!

ነቢውላ (ኬረን ጂላን)

አዉቅአለሁ ሁለትአችሁም እብድ እንደሆናችሁ።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

[በገሞራ ከመዳኑ ይልቅ ነቢውላ የተቀረቀረ እጇን መቁረጥ እና መከስከስ መረጠች።]

አይሆንም!

[ነቢውላ ተፈጥፍጣ ስትወድቅ ቆይታ አንድ የራቬጀር በራሪ መርከብ ላይ ወደቀች]

ባለመርከብ 

[በነቢውላ መለሰት ደነገጠ]

የምን አባ...?

ነቢውላ (ኬረን ጂላን)

ዉጣ!

[ራቬጀሩን ከመቅጽበተደ ሞዥልቃ በመመንጨቅ ከመርከቡ ዉጭ ወረወረችው]


ጨለማ አስተሩ ዉስጥ


[ገሞራ ኃይል ማስተላለፊያውን ዘግታ የድልድዩን በር ከፈተች እና ከጴጥሮስ፣ ድራክስ እና ግሩት ገቡ። ተጉዘው ጥቂት በሮኬት ልእለ-መድፍ ጴጥሮስ ሮናንን አጊንቶ ተኮሰበተት]

--------

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

አንቺ አደረግሽው!

[ሮናን ቢመታም አሁንም ህልው ነው። በድንገት ተነሳ እና የዉጊያ መዶሻውን ተገለገለ ያም ደቦውን ወደጎን ፈነገለ። ድራክስ፣ ወደ ሮናን ለማጥቃት ከነፈ። ዳሩ ሮናን አንገቱን አፈፍ አደረገው እና አንቆ በእጁ ወደላይ ከፍአድርጎ በመስቀል አንጠለጠለው]

 ሮናን (ሊ ፔስ)

[ላንጠለጠለው ድራክስ]

ተሳስቼ ነበር!

ቤተሰብህን አስታዉስ ዘንድ ነው!

ጩኸትዎችአቸው በጣም አሳዛኝ ነበር። እኔ...

[ወደ መርከቡ ሮኬት ከመርከቡ ጋር ሰርጎ ሮናን ጋር ተጋጨ እና ጣለው። እሮናን የተመታ ስለሆነ የሞተ መሰለ። የሮናን መርከብ ወደ ዉድመቱም እየተፋጠነ በመከስከስ ፍጥነት ተቀምጦ ሲሻገር ጓደኛዎቹ ሁሉ ተሰበሰበቡ። በመከስከሱ ስጋት ተከብበው ሲጠጋጉ፣ እነእርሱን ለማዳን ሲል፣ ግሩት በሰዉነቱ ሁሉ መጠበቂያ ክበብ አድርጎ መጋረጃ ጎጆ ፈጠረ እና ጓደኛዎቹን ሁሉ ማቀፍ ጀመረ]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

አይሆንም፣ ግሩት! አትችልም።

[እሚከውነውን ሁሉን የመክበብ እና ከመከስከሱ የማዳን ጥረትን ተመልክተለ ማልቀስ ጀመረ]

አንተ ትሞት አለህ።

ለምንድን ነው ይህን እምትከውነው?

ስለምን??

ግሩት (ቪን ዲዝል)

[ሁሉንም ሰበሰበ። ከሰዉነቱ ለጥጦ በአወጣአቸው ወፍራም እና ረዥም ሐረጎች ጎጆ ሰርቶ የተጎዱትንም ቀበቶ በመስራት ጓደኞቹን ሁሉ አቅፎ ሰበሰበአቸው።]

እኛ

ግሩት

ነን!

[በከበበው የሰውነቱ ጎጆ ዉስጥ መብራቶቹን ከሰውነቱ እንዲሁ አፍልቆ ለብርሃንነት አበራ]

[የሮናን ታንኳ ወደ ዋናውምድር ተፋጥኖ በመዉደቅ ተከሰከሠ እና ወደመ]

[ሁሉም በመርከቡ የነበረ በግሩት የታቀፈ ሁሉ ከመከስከሱ አደጋ መጎዳት ተረፈ፦ በቀረ ግሩት ፤ እርሱም የተዘራ የልምልም ክምር ሆኖ ታየ። ሮኬት ከልምልሙ የግሩት እሬሳ ጥቂት ስንጥሮች አነሳ እና በሀዘን አቅፎት እያነባ ተመለከተ]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ደደብ ብዬ የጠራሁት ነበር!

[ሮናን ከወደመው መርከቡ ፍርስራሽ ወጣ፣ ገና አልሞተም። ሮኬት ሲመለከተው ገና ደሙ ፈልቶ ሊፋለመው በግኖ ወደ እርሱ ከነፈ]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ግሩትን ገደልክው!

[ሮናን ኮስሚ-ሮዱን ተገልግሎ ሮኬትን ወደጎን ወርዉሮ ፈጠፈጠ እና ጎዳው]

ሮናን (ሊ ፔስ)

[ወደ ዛንዳር መናገሻ ከተማዋ እየተመለከተ ለህዝቡ]

እነሆን! የእናንተ ቤተክዋክብቱ ጋሻጃግሬዎች። ምን ፍሬ ሰርተው ጨረሱ? ብቻ የእኔ አባት እና የእሱ አባት እና የእሱ በመጨረሻም በቀልን ሊያስቧት ይገባ ዘንድ ሆነ እንጂ! የዛንዳር ህዝብዎች ሆይ፣ ጊዜው መጥቶ አለ፦ ዋጋቢስ አማልክቶችአችሁን ተደስታችሁብአቸው ልትተዉአቸው ይሆን ዘንድ! እነሆ መዳኛአችሁ በእጅ ላይ ነው!

[የእጁ መዶሻን በሁለቱም እጆቹ ጨብጦ የጥፋቱን ፈር ሊቀድድ ምድሩን ሊመታ በአየሩ ተዘጋጀ]

[ከተመታበት ተነስቶ በምስጢር ሮናንን ለመተኮስ መሳሪያ ለእሚሰራው፣ ለሮኬት ጊዜ ለመስጠት ጴጥሮስ መደነስ እና መዝፈን ጀመረ። ዛንዳርን ሊደመስስ እሚፈልግ የሮናን ድርጊትን ለማቋረጥ በቃ]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

“ዑ…ቻይልድ…

ቲንግስ አር ጎና ጌት ኢዚየር….

ዑ...ቻይልድ….

ቲንግስ ዊል ጌት ብራይተር።”

[ምድሩን በኮስሚ-ሮዱ መትቶ ማጥፋቱን በመጨረሻ አቋርጦ እሱን በመገረም መመልከት ለጀመረው ሮናን]

እነእዚህን ቃሎች አዳምጥ!

“ዑ...ቻይልድ...

ቲንግስ አር ጎና ቢ ኢዚየር...

ዑ...ቻይልድ...

ቲንግስ ዊል ጌት ኢዚየር።”

አሁን ደግሞ በከፍታ አሟሙቀው!

[መደነሱን በማበርታት ቀዉጢ አደረገ]

“ሰም ዴይ...

ዊ ዊም ጌት ኢት ቱጌዘር...

ኤንድ ዊ ዊል ጌት...”

ሮናን (ሊ ፔስ)

 [ተገርሞ መበሳጨት ጀመረ]

ምን እያደረግህ ነው?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ዳንስ-ፍልሚያ፣ ወንድም።

እኔ እና አንተ¡

[ገሞራን ለመደነስ እጅ ልኮ ጋበዛት]

ገሞራ!

[ገሞራ አናቷን በእንቢታ ነቀነቀች]

ጮሌ!

መልሰህ መዉሰድ።

[መደነሱን ባለማስነቃቱ ሆኖ ቀጠለ]

ሮናን (ሊ ፔስ)

[እጅግ ተናደደ]

ምን...እያደረግህ...ነው!?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እኔ አንተን እያወዛገብኩ ነው፣ አንት ትልቅ እበት ላይ የበቀልክ አናዳጅ!

[ድራክስ እና ሮኬት ከሮናን ጎን ተገለጡ እነእሱም ልእለ-መድፉን ወደ ዉጊያመዶሻው ተኮሱ ያም ምት ድንጋዩን ከመዶሻው ባነርነት ፈታ። ከዛ ሁለቱም ሮናን እና ጴጥሮስ፣ ከተፈጨው የሮናን መዶሻ ሲወድቅ የነበረ ድንጋዩን ለመጨለፍ ተሽቀዳድመው ሄዱ]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

አይሆንም!

[ጴጥሮስ ድንጋዩን ለቀመ እና በድንጋዩ ጉልበት እየተወረሰ ይነድድ ጀመረ] 

ገሞራ (ዞይ ሶልዳና)

ጴጥሮስ!

ዉሰድ እጄን!

[ልክ ጴጥሮስ እየተቃጠለ ወደ እሷ ዞሮ ሲመለለት መልሽጫወታ (ፍላሽባክ) አደረገ ያም እናቱ ልትሞት ስትል እጇን በሞት አልጋ ላይ እንደጋበዘችው ነበር]

ሜሪዴት ክዊል (ሎዉራ ሀዶክ)

እጄን ዉሰድ፣ ጴጥሮስ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

[ስቃይ ዉስጥ ሆኖ የገሞራ የተዘረጋ እጅ ዉስጥ የእናቱን ሞት አልጋ ጥሪ ተመለከተ]

እማ!

ገሞራ (ዞይ ሶልዳና)

እጄን ዉሰድ!

[በዓይኖቹ እንባዎች ይዞ እያወረደ ጴጥሮስ የገሞራ እጅን ወሰደ፣ ገሞራ የድንጋዩን ጉልበት ቃጠሎ ተጋራችው እና መንደድ ጀመረች። ድራክስ ከእዛ የጴጥሮስ ትከሻ ላይ በሌላው ጎኑ እጁን አኖረበት እና እርሱም የበለጠ እየሆነ የእሚሄድ ድንጋይ ጉልበት ተጋራ እና መንደድ ጀመረ። ሦስቱም ሲነድዱ፧ እዲሁ የድራክስን እጅ ደግሞ ሮኬት ተንጠራርቶ ወሰደ። ተቃጠለ እና ጮኸ። በጋራ ሆነው የድንጋዩን ጉልበት ተጋሩ እና በአራትአቸው መሀከል ተጣጣ። ሳያወድምአቸው ቀረ]

ሮናን (ሊ ፔስ)

[ሮናን ባለመሞትአቸው ተገረመ]

ኢሟችዎች ናችሁ!

እኮ እንዴት?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አንተው አልክው እራስህ፣ ዉሻዋ። እኛ የቤተክዋክብቱ ጋሻጃግሬዎች ነን።

[በጋራ በድንጋዩ ጉልበት ሮናንን አወደሙት እና ገሞራ ሩሩን ድንጋዩን ለመሸብለል ተገለገለች]

---

[ሁሉም የአካባቢው ዛንዳርአዊ ተደሰተ]

[ድህረ ሮናን ውድመት እና ድንጋዩ በሩሩ መጠቅለል፣ ጴጥሮስ ወደ ገሞራ ፊት ዞረ ያኔም ዮንዱ እና ደቦው ተከሰቱ]

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

ደግ፣ ደግ፣ ደግ። ልክ የመብራቱ ትርዒት።

[ህህታ አቀረበ]

ጣፋጭ ይህ አይደለምን? ዳሩ አንድ እምትከታተለው ጉዳይ አለህ ጉሮወሸባው፣ አንሶላ-መጋፈፉ ከመጀመሩ በፊት።

[ስለ ሩሩ እያሳበቀ]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ጴጥሮስ፣ አታደርገዉም። ጴጥሮስ።

[እንዳያስረክበው አሳሰበች]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ይህን ዳግ-ማገነዛዘብ አለብህ፣ ዮንዱ። ይህንን ለማን እንደምትሸጠው እማውቀው ነገር አይደለም፣ ዳሩ ህዋው እሚሰነብተው ለኖቫ ጓዶች እምትሠጠው ከሆነ ነው።

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

እኔ እንደ አንድ መልአክ ቆንጅዬ ልሆን እችል አለሁ፣ ግን በእርግጠኛነት አንዱን ግን አይደለሁም። አስረክበው፣ ልጄ። 

[አቅማምቶ ጴጥሮስ ሩሩን ለዮንዱ አስረከበ፣ እርሱም ደቦውን ለመመለስ ዕዝ አድርጎ በሀሴት ዞረ]

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ዮንዱ?

[ዮንዱ ጴጥሮስን ለመመልከት ዞረ]

ያን ሩር አትክፈት! ያን ታዉቅአለህ፣ አይደለም?

ህዝቦች ላይ ምን እንደእሚያደርግ አይተህው አለ።

[ዮንዱ ፈገግ ብሎ ተመልክቶት ተመልሶ በመዞር አቀና]

--------

[ወደ ዮንዱ ህዋመርከብ ፣ ራቬጀሮቹ በቅንጦት እየተጫኑ በመንሳፈፍ አዘቅዝቀው ወደ ጴጥሮስ ተመለከቱ]

ክራግሊን (ሲያን ጉን)

አዎን፣ ክዊል ደህና ሆኖ ተገኝቶ አለ። ምንአልባት መልካም ነው ፣ እንድናደርገው እንደተቀጠርንው ለአባቱ ስላላስረከብንው። 

ዮንዱ ዑዶንታ (ሚካኤል ሩከር)

አዎ፣ ያ ሰዉ አህያ ነበር። 

[መርከብአቸው ተመነጠቀ]

--------

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

[ለገሞራ]

ሩሯን እሱ ላይ እንደለወጥኩበት ገሃዱን-ሲገነዘብ ይበሳጭ ዘንድ እሚሆን ነው። 

[ጴጥሮስ ባለድንጋዩ ሩሩን ያዘ። እና ገሞራ ሳቅ አለች]

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ሊገድልህ ነበር፣ ጴጥሮስ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አዉቅአለህ።

ዳሩ ብቸኛው የነበረኝ ቤተሰቤ ነገር ነበር።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

አአይ። አልነበረም!

[ሮኬት በግሩት ስንጥርጥሮች ክምር በእዚያ ተቀምጦ እያነባ ነበር ልክ ድራክስ በእዚያው አጠገቡ ተዘረፈጠ እና አናቱን አሸት አሸት በማድረግ ሀዘኑን ተጋራ ያም ሊያጽናናው አስቦ ነበረ]

[ጴጥሮስ እና ደቦው በኖቫ ዋና ቅርንጫፍ ተገኙ]

--------

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ሲጀመር ለምን ይህን ማወቅ ይገባቹህ ዘንድ አለ?

ኮርፕስማን ዴይ (ዮሐንሥ ሲ/ሬሊ)

ስናስርህ፣ በህብለሰረሰር ስነስርአትህ አንድ አፈንጋጭ-ትንግርት አስተዋልን፣ እና እንዲፈተሽ አደረግንው።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ታራንአዊ አይደለሁም?

ኖቫ ቀዳሚት (ግሌን ክሎስ)

ኩርማን ታራን ነህ። እናትህ ከምድር ነበረች። ያንተ አባት፣ ዳሩ፣ ቀድሞ ያልተመለከትንው የሆነ በጣም ጥንትአዊ ነው።

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ለዚያ ይሆን አለ ድንጋዩን አርዝመህ የያዝክውን ያክል ለመቆየት የቻልክበት አመክዮ።

[አንድ በር ተከፈተ፣ ድራክስ ከሮኬት ጋር እንደአለ ተቀላቀሉአቸው እሱም ዉስጡ ሚጢጢ ግሩትን ተክሎበት የነበረ ማሰሮን ይዞ አለ]

ኖቫ ቀዳሚት (ግሌን ክሎስ)

ጓደኛህ ደርሶ አለ። በኖቫ ጓዶች በኩል ሆነን፣ ጥልቅ ምስጋናአችንን ለመግለጽ እንወድድ አለን ዛንዳርን ለመቆጠብ ላደረጋችሁት እርዳታ። ዴናሪያን ዴይን ብትከተሉት፣ አንድ እሚያሳያችሁ ነገር አለ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እናመሰግን አለን፣ ኖቫ ቀዳሚት።

[ደቦው ዴይን እየተከተሉ፣ ገሞራ ድራክስ ጎን መራመድ ጀመረች]

--------

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ያንተ ሚስት እና ልጅ በደህና ሰላም ያርፉ አለ እንደተበቀልክልአቸው በመገንዘብ።

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

አዎን። በእርግጥ፣ ሮናን አንድ አሻንጉሊት ብቻ ነበር። እንደምሩ ከሆነ ታኖስን ነው መግደል እሚፈልገኝ።

[ደቦው ዴይን ተከትሎ ውጭ ወጣ እሱም የታደሰ ሚላኖው ጋር አገናቸአቸው]

--------

ኮርፕስማን ዴይ (ዮሐንሥ ሲ/ሬሊ)

እኛ እንደ ብሉዩ የቀረበ እቅጭ እንዲሆን በተቻለ ሁሉ ሞክረን ነበር። የምንችለውን ያክል ከመፈራረስ አድነንው ነበር።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እንዴ እኔ... 

[ጴጥሮስ በአየው የወደመው ሚላኖው እድሳት ኖቫዎች ያዘጋጁለትን አዲስ ሚላኖውን እየተመለከተ በመደነቅ ሆኖ ቃልዎች አጥረውት ታየ]

አመሰግንአለሁ።

ኮርፕስማን ዴይ (ዮሐንሥ ሲ/ሬሊ)

ቤተሰብ አለኝ። በህይወት ያሉት ባንተ የተነሳ ነው!

[እየተራመዱ መልእንቶቹን መንገር ቀጠለ]

የወንጀለኛ ማህደርህ ተሠርዞ አለ።

ቢሆንም ግን፣ በመጪው ጊዜ ምንም ህግ ከመጣስ እማስጠነቅቅህ ነኝ።

[ሮኬት ማሰሮውን ይዞ መሀልአቸው ጨዋታውን ተቀላቀለ]

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ጥያቄ።

ለመዉሰድ እምፈልገውን አንድ ነገር ብመለከት፣ እና የሆነ የሌላ ሰው ንብረትነት ቢሆንስ?

ኮርፕስማን ዴይ (ዮሐንሥ ሲ/ሬሊ)

እምትታሰር ይሆን አለ!

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ዳሩ ያንን ከያዘው ሰው የበለጠ እምፈልገው ቢሆንስ፣ ሰውየው?

ኮርፕስማን ዴይ (ዮሐንሥ ሲ/ሬሊ)

እስከአሁን ኢህግአዊ ነው።

ሮኬት (ብራድሊ ኩፐር)

ያን አምጠየኩህም።

እኔ የበለጠ ነው እምፈልገው፣ ጌታዬ። ይገባህ አለ?

[በተናገረው እምትስቅ ገሞራ ላይ ተመለከተ]

ምን ላይ ነው እምትስቂው? ለምን? ከእዚህ ኩሩሰው ጋር ዉይይት መያዝ አልችልም?

[ወደ ሚላኖው እምታዘግም ገሞራን ተቀላቀሎ አብረው ተጓዙ]

ድራክስ (ዳዊት ባዉቲስታ)

[ከጀርባ በእነ ዴይ እና ጰሔጥሮስ ላይ ደረሰብአቸው]

አንድ ሰው የሆነ እሚያበሳጭ ነገር ቢከውን እና ሰረሰሩን ልነቅለው ብወስንስ?

ኮርፕስማን ዴይ (ዮሐንሥ ሲ/ሬሊ)

ያ እማ... ያ በእርግጥ ግድያ ነው። ያ ከወንጀሎች ሁሉ ከከፉት አንዱ ነው። እንዲሁ... እና ኢህግአዊ ነው።

[ወደ ሚላኖው መንገዱን እያቀና በመልሱ አቅማማ]

ድራክስ (ዳዊት ባውቲስታ)

ህምምም...

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

ደህና ይሆኑ አለ፣ ዴይ። ዓይን እጥልብአቸው አለሁ!

ኮርፕስማን ዴይ (ዮሐንሥ ሲ/ሬሊ)

አንተ?

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

አዎን። እኔ!

[ተሰናብቶ ጴጥሮስ ሚላኖው ውስጥ ገባ። ቅድመሞቷ እናቱ ያስረከበችውን ሥጦታ፣ በመጨረሻ ደፍሮ ከፈተው እና አነበበ]

--------

ሞት ላይ ያለች የ ጴጥሮስ እናት (ሎውራ ሀዶክ)

 [በድምጽ ሆና]

ጴጥሮስ፣ እኒህ የመጨረሻ ጥቂት ወሮች ለአንተ እንደከበዱህ አውቅ አለሁ። ዳሩ፣ እኔ ወደ ተሻለሥፍራ እምዘምት ነኝ እና እኔ ደህና እሆን አለሁ። እና ሁልጊዜም ከአንተ ጋር እሆን ዘንድ አለሁ። አንተ የህይወቴ ብርሃን ነህ። የእኔ ብርቅ ልጅ። የእኔ ኮከብ-ጌታ። ፍቅር፣ እማ።

 [ጴጥሮስ ሥጦታውን ፈለቀቀ እና ሌላ "ድንቅ ዉህድ" ድምጽአጫዋች እንደሆነ ተመለከተ። ድምጽማጫወቻውን በመርከቡ ካሴት መቅረጫ ነከረው እና አጫዉትልኝ ቁልፉን ጠቅታ ከወነበት]

“ኤይን ኖ ማውንቴን ሀይ ኢነፍ" 

[“የማርቪን ጋዬ እና ታሚ ተረል ዜማ ተንቆረቆረ። ገሞራ ወደ ጴጥሮስ ተራመደች እና እርስለእርስአቸው ፈገግታ ተመላለሱ።]


በዮንዱ መርከብ ዉስጥ


[ሁሉም ድህረ-ድል የጠጡ  ሲያውካኩ ዮንዱ ተቀምጦ በሃሳብ ተወስዶ ነበር። ተመልሶ ከሃሳቡ ዮንዱ ሩሩን ደፍሮ ሲከፍት እንመለከት ሆንን። ዉስጡ ግን ኁልቆመሣፍርት ድንጋዩ የለም። አንድ ትሮል አሻንጉሊትን ፈለገ። ሳቀበት ያም በራሱ ነበር]


ዛንዳር ዉስጥ


[ዴይ ወደቤቱ ተመለሰ። እና ሚስቱ እና ሴት ልጁ ጋር በሀሴት ተገናኘ]

[ማብቂያ መስመርዎች ፤ ጴጥሮስ እና ሌላዎቹ ለመብረር ሲያኮበኩቡ፣ ድራክስ ሮኬት ላይ ፈገግ አለ። እርሱም በትንሹ የማሰሮው ጓደኛው ግሩት ላይ እሚመለከት ነበር። እርሱም በማሰሮው ሆኖ ከመተኛቱ መንቃቱ ነበር እና አፋሸከ] 

--------

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

እና፣ ቀጣይ ምን ብንከውን ይሻለን ዘንድ ነው?

የሆነ ደግ ነገር? የሆነ ክፉ ነገር? ትንንሽ ከሁለቱም?

[ለሁሉም ስለቀጣየደ ሁኔታአቸው ሀሳብ አቀረበ። እነእርሱም ቤተሰብ ሆነው ከብበው ነበሩ] 

ገሞራ (ዞይ ሳልዳና)

ያንተን ምሪት እንከተለው አለን፣ ኮከብ-ጌታ።

ጴጥሮስ ክዊል (ክሪስ ፕራት)

[መልስ ከመመለሱ ቀደም ብሎ ጴጥሮስ ፈገግ አለ]

ከሁለቱም ጥቂት ጥቂት!

[ሚላኖውን አብርሮ አነሳ ያም ከጃክሰን ፭ዎቹ ዘፈን "አይ ዋንት ዩ ባክ" ጋር እየተጫወተ ሆነ]


የቤተክዋክብቱ ጋሻዎች እሚመለስ ነው።


ተፈጸመ፨


ዕዉቂያ (ክሬዲት)፨

[ዕዉቂያው ሲዘምት ጥቂት አደግ ያለ ግሩትን ከሙዚቃው ጋር ማሰሮው ውስጥ ወዝወዝ ሲል ተመለከትን። ድራክስ ቢላዋውን እያጸዳ በጎኑ ተቀምጦ ነበረደ። ግሩት ሲጨፍር ዞር የተመለከተ መስሎት ከቢላዋው ማጽዳት ወደ ማሰሮው ዞር ብሎ ሲመለከተው ግሩት ያቋርጥ እና ቀጥ ብሎ ባለበት ይቀዘቅዝ አለ። ከዛ ድራክስ ወደ ቢላዋው ማጽዳቱ ሲዞር ግሩት ዳግ-መወዛወዝ አደረገ። ድራንስ እንቅስቃሴ ያየ መስሎት አሁንም ዞሮ ዳግ-ሲያየው ግሩት ባለበት ቅዝቅዝ አለ ደግሞ።]


ድህረ-ዕዉቂያ ገቢር (ፖስት ክሬዲት ሲን)፨


-----

ምንሙሥፍራ ዉስጥ


ታለኒር ቲቫን ሰብሳቢው (ቤኒሲዮ ዴል ቶሮ)

[የወደመ ቤተመመዝገቢያ ዉስጥ ስሜት በማጣት ተቀምጦ ሰብሳቢው ታየ። መጠጥ በመማግ ይጠጣ አለ። በህይወት የተረፈ ክፍት የፈለከኛ-ጭምብል አጥላቂ ዉሻ መጥቶ ፊቱን ላሰው]

ዝዩ ሀዋርድ (ለባሼሰብእ (አንትሮፖሞርፊክ) ዝይ፣ ሴት ግሪን)

ስለምን እንዲያ እንዲልስህ ብለህ አደረግህ?

[ተሰብሮ የተከፈተ ማፈኛ ብረት (ኬጅ) ላይ ተቀምጦ ዝዩ ሀዋርድን እንመለከተው ዘንድ ሆነ፣ እርሱም እሚጠጣትን ብርጭቆ ለእራሱ በእጁ የጨበጣት ነበረ]

ዝዩ ሀዋርድ (ለባሼሰብእ (አንትሮፖሞርፊክ) ዝይ፣ ሴት ግሪን)

ቀፋፊ!

[ማግ አድርጎ ከድምጽ ጋር ፉት አደረገ]

ዝዩ ሀዋርድ ለባሼሰብእ (አንትሮፖሞርፊክ) ዝይ፣ ሴት ግሪን)

ኡኸይ!

ሲወርድ ቃጠል ያደርግ አለ።


የቤተክዋክብቱ ጋሻጃግሬዎች

ፍፃሜው ሆነ፨


Comments

Popular posts from this blog

SOME POPULAR ETHIOPIAN SAYINGS AND PROVERBS WITH THEIR TRANSLATION AND EXPLANATION IN ENGLISH. 2

SOME POPULAR ETHIOPIAN SAYINGS AND PROVERBS WITH THEIR TRANSLATION AND EXPLANATION IN ENGLISH.1

SOME POPULAR ETHIOPIAN SAYINGS AND PROVERBS WITH THEIR TRANSLATION AND EXPLANATION IN ENGLISH. 8